የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አዲስ አበባ የአፍሪካ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፎረምን ታስተናግዳለች

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦ ስምንተኛው የአፍሪካ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፎረም ሚያዚያ 18 እና 19 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ያዘጋጀው ፎረም “ አጀንዳ 2030 እና አጀንዳ 2063ን በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ዲጂታል ኢኖሼሽን ውጤታማ ማድረግ” በሚል መሪ ሀሳብ ይካሄዳል።

ፎረሙ የአፍሪካ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ኢኖቬተሮች እና የልማት አጋሮች በአንድ መድረክ ያገናኛል።

ባለድርሻ አካላቱ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ በአፍሪካ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ያለውን ሚና አስመልክቶ በፎረሙ ይመክራሉ።

መድረኩ የአፍሪካ የኢኖቬሽን አጀንዳን የበለጠ ለማራመድ የሚያስችል ቁልፍ ማዕቀፍ ሆኖ እንደሚያገለግልም ኢዜአ ከኢሲኤ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

በመንግስት፣ በአካዳሚክ ማህበረሰቡ፣ በኢንዱስትሪ እና ዓለም አቀፍ ተቋማት መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ውይይት ይደረጋል።

ፎረሙ አፍሪካ በዘላቂ ልማት ግቦች የደረሰችበትን የአፈጻጸም ደረጃ ይገመግማል።

ውሃ እና ንጽህና፣ ተመጣጣኝ እና ንጹህ ኢነርጂ፣ ኢንዱስትሪ እና መሰረተ ልማት፣ ዘላቂ ከተሞችና የልማት አጋርነት ጨምሮ የተለያዩ የዘላቂ ልማት ግቦችን የተመለከተ ውይይት ይካሄዳል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች ኢኖቬሽን ተኮር መፍትሄዎች እና ቀጣናዊ ትብብርን ማጠናከር የሚያስችሉ የተግባር እርምጃዎች ላይ ምክረ ሀሳባቸውን ያቀርባሉ።

በፎረሙ ላይ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጨምሮ ከፍተኛ አዎንታዊ ለውጥ ያመጡ ቴክኖሎጂዎች፣ ጀማሪ የስራ ፈጠራዎች (Startups)፣ የምርምር ኢኒሼቲቮች እና የኢኖቬሽን ማዕከላት ስራዎች ለእይታ ይቀርባሉ።

ኹነቱ የእውቀት ሽግግርን ለማሳለጥ፣ በዩኒቨርሲቲዎች እና ምርምር ተቋማት መካከል ያለውን አጋርነት ማጠናከር እንዲሁም በአፍሪካ ያለውን የቴክኖሎጂ ሽግግር የመደገፍ አላማ አለው።

በፎረሙ ላይ የአፍሪካ ሀገራት መንግስታት ተወካዮች፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አመራሮች፣ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን፣ የትምህርት ተቋማት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የአፍሪካ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፎረም ውጤቶች በአዲስ አበባ የሚካሄደውን 12ኛው የአፍሪካ ቀጣናዊ የዘላቂ ልማት ፎረም የሚደግፉ መሆናቸው ተመላክቷል።

12ኛው የአፍሪካ ቀጣናዊ የዘላቂ ልማት ፎረም ከሚያዚያ 20 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026