🔇Unmute
አዳማ፤መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦በፌዴራልና በክልሎች መካከል ያለውን የጋራ ገቢ ክፍፍል ፍትሃዊ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ውጤት ማምጣታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር አስታወቁ።
ምክር ቤቱ በበይነ-መንግሥታት የፌዴራል ግንኙነትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በመድረኩ ላይ እንዳስታወቁት፤ የምክር ቤቱ አንዱና ዋነኛው ተግባር ፍትሃዊ ልማትና ዕድገት እንዲኖር ማስቻል ነው።
ለዚህም ተፈጻሚነት ባለፉት አምስት ዓመታት አዳዲስ አሠራሮችን የመዘርጋትና ነባሮቹን የማሻሻል ተግባራት ሲከናወኑ ቆይተዋል ብለዋል።
በተለይም በጋራ ገቢዎች ክፍፍል ቀመር ላይ የተደረገው መሠረታዊ ማሻሻያ የክልሎችን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን ጠቁመዋል።
"ከማሻሻያው በፊት 4 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ብቻ የነበረው የክልሎች የጋራ ገቢ ድርሻ፤ በ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ወደ 91 ነጥብ 73 ቢሊዮን ብር እንዲያድግ ተደርጓል" ብለዋል።
ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው የገቢዎች ሚኒስቴር የገቢ ዝውውርን የሚያፋጥን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት በመዘርጋቱና የምክር ቤቱን ውሳኔዎች በፍጥነት ወደ ተግባር በመቀየሩ መሆኑን አመልክተዋል።
ከዚህ ባለፈም ከከፍተኛ ማዕድን ሀብቶች የሚሰበሰበው የሮያሊቲ ገቢ ክፍፍልም መሻሻል ማሳየቱን ገልጸዋል።
ምንም እንኳ አመርቂ ውጤቶች ቢመዘገቡም አሁንም ያልተሻገርናቸው ተግዳሮቶች መኖራቸውን ያነሱት አፈ ጉባኤው፣ በተለይም ከፌዴራል ተቋማት ወደ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የሚተላለፉ ድጎማዎች ላይ የአሳታፊነትና የግልጸኝነት ክፍተቶች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።
ሥልጠናው እነዚህን ክፍተቶች ለመሙላት እንደሚያግዝም አስረድተዋል።

በምክር ቤቱ የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ አቶ ኃይሉ ኢፋ በበኩላቸው፤ ምክር ቤቱ የዜጎችን ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የሕግ ማዕቀፎችንና ግልጽ የአሠራር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የስልጠና መድረኩም በሀብት ክፍፍል ሥርዓቱ ላይ መተማመንን በመፍጠር ለፌዴራል ሥርዓቱ መጠናከር የጎላ ሚና እንደሚኖረው አስታውቀዋል።
በመድረኩ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026