🔇Unmute
አዳማ፤መጋቢት 9/2018 (ኢዜአ)፦በፌዴራልና በክልሎች መካከል ያለውን የጋራ ገቢ ክፍፍል ፍትሃዊ ለማድረግ የተሰሩ ስራዎች ውጤት ማምጣታቸውን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር አስታወቁ።
ምክር ቤቱ በበይነ-መንግሥታት የፌዴራል ግንኙነትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በመድረኩ ላይ እንዳስታወቁት፤ የምክር ቤቱ አንዱና ዋነኛው ተግባር ፍትሃዊ ልማትና ዕድገት እንዲኖር ማስቻል ነው።
ለዚህም ተፈጻሚነት ባለፉት አምስት ዓመታት አዳዲስ አሠራሮችን የመዘርጋትና ነባሮቹን የማሻሻል ተግባራት ሲከናወኑ ቆይተዋል ብለዋል።
በተለይም በጋራ ገቢዎች ክፍፍል ቀመር ላይ የተደረገው መሠረታዊ ማሻሻያ የክልሎችን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደጉን ጠቁመዋል።
"ከማሻሻያው በፊት 4 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ብቻ የነበረው የክልሎች የጋራ ገቢ ድርሻ፤ በ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ወደ 91 ነጥብ 73 ቢሊዮን ብር እንዲያድግ ተደርጓል" ብለዋል።
ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው የገቢዎች ሚኒስቴር የገቢ ዝውውርን የሚያፋጥን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት በመዘርጋቱና የምክር ቤቱን ውሳኔዎች በፍጥነት ወደ ተግባር በመቀየሩ መሆኑን አመልክተዋል።
ከዚህ ባለፈም ከከፍተኛ ማዕድን ሀብቶች የሚሰበሰበው የሮያሊቲ ገቢ ክፍፍልም መሻሻል ማሳየቱን ገልጸዋል።
ምንም እንኳ አመርቂ ውጤቶች ቢመዘገቡም አሁንም ያልተሻገርናቸው ተግዳሮቶች መኖራቸውን ያነሱት አፈ ጉባኤው፣ በተለይም ከፌዴራል ተቋማት ወደ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የሚተላለፉ ድጎማዎች ላይ የአሳታፊነትና የግልጸኝነት ክፍተቶች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።
ሥልጠናው እነዚህን ክፍተቶች ለመሙላት እንደሚያግዝም አስረድተዋል።

በምክር ቤቱ የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ቋሚ ኮሚቴ ጸሐፊ አቶ ኃይሉ ኢፋ በበኩላቸው፤ ምክር ቤቱ የዜጎችን ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የሕግ ማዕቀፎችንና ግልጽ የአሠራር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የስልጠና መድረኩም በሀብት ክፍፍል ሥርዓቱ ላይ መተማመንን በመፍጠር ለፌዴራል ሥርዓቱ መጠናከር የጎላ ሚና እንደሚኖረው አስታውቀዋል።
በመድረኩ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የድጎማ በጀትና የጋራ ገቢዎች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ እንዲሁም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025