🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ፤መጋቢት 9/ 2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ያለልዩነት በአቋም መስራት የግድ መሆኑን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ፣ ታሪክን፣ መልካአ ምድርን እንዲሁም ዓለም አቀፍ እውነታን በመያዝ የቀጠለ የዲፕሎማሲ ጥረት መሆኑ ይታወቃል።
ከአፍሪካ በህዝብ ብዛት በሁለተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ኢትዮጵያ ከባህር ተገፍታ እና ተገልላ መኖር የለባትም በሚል የባህር በር ጉዳይ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል።
በአንድ ወቅት የባህር በር ባለቤት የነበረች ሀገር እንዴትና ለምን አጣች የሚለው ጉዳይም የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ የሚነሳ ጉዳይ ሆኗል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ያለልዩነት በአቋም መስራት የግድ መሆኑን ምሁራን ያስረዳሉ።
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት አልማዝ ባልታ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ ያለባህር መግቢያ መውጫ ህልውናዋ አደጋ ላይ የሚወድቅ በመሆኑ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ መምጣቱ ተገቢ መሆኑን አንስተዋል።
የህዝብ ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ፤ የምጣኔ ሃብቷ በእጅጉ እያደገ መሆኑ እንዲሁም ቀጣናዊ ትስስርን ከማሳለጥ አንፃር ኢትዮጵያ የባህር መውጫና መግቢያ ያስፈልጋታል ብለዋል።
በመሆኑም ጥያቄው የተገቢነት ማሳያ የሚሆኑ ተጨባጭና አሳማኝ ምክንያቶች ያሉት በመሆኑ ተገቢው ምላሽ እስከሚሰጥ ድረስ ጥያቄያችን ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።
የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄው የብሄራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ያለምንም ልዩነት በጋራ የምንቆምለት አጀንዳችን ሆኖ መዝለቅ አለበት ብለዋል።
በዚህ ረገድ በተለይም ምሁራን በጥናትና ምርምር ጭምር የተደገፉ ጽሁፎችን በማሳተም የላቀ ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸውም አንስተዋል።
በዩኒቨርሲቲው የቋንቋ እና ስነ ፅሁፍ ትምህርት ክፍል መምህርትና ተመራማሪ ደነቁ አበረ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ እየሄደችበት ያለው የዕድገት ግስጋሴ ከራሷ አልፎ ለቀጣናው አገራትም የጋራ ተጠቃሚነት ጉልህ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም ጠንካራ ትስስር ለመፍጠር የባህር በር ማግኘቷ የግድ መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ ካላት የህዝብ ብዛትና ለቀይ ባህር ካላት ቅርበት፣ ከታሪክና ከመልካአ ምድር አንፃር የባህር በር ማግኘት የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ያለልዩነት በአቋም መስራት የግድ ይላል በማለት ምሁራኑ አፅኖት ሰጥተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025
አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...
Feb 12, 2025