የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ ነው

Mar 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ፤መጋቢት 9/ 2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ያለልዩነት በአቋም መስራት የግድ መሆኑን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለጹ።


የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ፣ ታሪክን፣ መልካአ ምድርን እንዲሁም ዓለም አቀፍ እውነታን በመያዝ የቀጠለ የዲፕሎማሲ ጥረት መሆኑ ይታወቃል።


ከአፍሪካ በህዝብ ብዛት በሁለተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው ኢትዮጵያ ከባህር ተገፍታ እና ተገልላ መኖር የለባትም በሚል የባህር በር ጉዳይ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል።


በአንድ ወቅት የባህር በር ባለቤት የነበረች ሀገር እንዴትና ለምን አጣች የሚለው ጉዳይም የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ የሚነሳ ጉዳይ ሆኗል።


በመሆኑም የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ያለልዩነት በአቋም መስራት የግድ መሆኑን ምሁራን ያስረዳሉ።


በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት አልማዝ ባልታ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ ያለባህር መግቢያ መውጫ ህልውናዋ አደጋ ላይ የሚወድቅ በመሆኑ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ መምጣቱ ተገቢ መሆኑን አንስተዋል።


የህዝብ ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ፤ የምጣኔ ሃብቷ በእጅጉ እያደገ መሆኑ እንዲሁም ቀጣናዊ ትስስርን ከማሳለጥ አንፃር ኢትዮጵያ የባህር መውጫና መግቢያ ያስፈልጋታል ብለዋል።


በመሆኑም ጥያቄው የተገቢነት ማሳያ የሚሆኑ ተጨባጭና አሳማኝ ምክንያቶች ያሉት በመሆኑ ተገቢው ምላሽ እስከሚሰጥ ድረስ ጥያቄያችን ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።


የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄው የብሄራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ያለምንም ልዩነት በጋራ የምንቆምለት አጀንዳችን ሆኖ መዝለቅ አለበት ብለዋል።


በዚህ ረገድ በተለይም ምሁራን በጥናትና ምርምር ጭምር የተደገፉ ጽሁፎችን በማሳተም የላቀ ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸውም አንስተዋል።


በዩኒቨርሲቲው የቋንቋ እና ስነ ፅሁፍ ትምህርት ክፍል መምህርትና ተመራማሪ ደነቁ አበረ (ዶ/ር)፤ ኢትዮጵያ እየሄደችበት ያለው የዕድገት ግስጋሴ ከራሷ አልፎ ለቀጣናው አገራትም የጋራ ተጠቃሚነት ጉልህ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።


በመሆኑም ጠንካራ ትስስር ለመፍጠር የባህር በር ማግኘቷ የግድ መሆኑን አንስተዋል።


ኢትዮጵያ ካላት የህዝብ ብዛትና ለቀይ ባህር ካላት ቅርበት፣ ከታሪክና ከመልካአ ምድር አንፃር የባህር በር ማግኘት የትውልዱ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል።


በመሆኑም የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የብሄራዊ ጥቅምና የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ያለልዩነት በአቋም መስራት የግድ ይላል በማለት ምሁራኑ አፅኖት ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026