የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት ሰጥቷል

Mar 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሚያስችል የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ራቢ (ኢ/ር) ገለጹ።

የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ እና ጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ኢንቨስትመንትስ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።


ስምምነቱ በኢትዮጵያ በኢነርጂ ዘርፍ የክህሎት ልማትን፣ ኢኖቬሽን እና ዘላቂ የኢነርጂ ልማትን ለማሳደግ ያለመ እንደሆነ ተመላክቷል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ስምምነቱ ለዩኒቨርሲቲው ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ አለው።

በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የንድፈ ሐሳብ ትምህርትን ከኢንዱስትሪው የተግባር ልምድ ጋር በማቀናጀት ለሀገር ግንባታ የሚሆኑ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ የሚያካሂዳቸው ጥናትና ምርምሮች ለጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ፕሮጀክቶች ግብዓት ከመሆናቸው ባሻገር ከኩባንያው የሚገኘው ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ዕውቀት ለተማሪዎችና ለሀገር የኢነርጂ ዘርፍ ትልቅ አቅም ይፈጥራልም ነው ያሉት።

ዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሚያስችል የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት መስጠቱን እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል።


የጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ኢንቨስትመንትስ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ፕሬዚዳንት ሱን ዦንግ እንዳሉት፤ ስምምነቱ በቻይና እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የኢንዱስትሪ እና የትምህርት ትስስር ለማሳደግ የሚያስችል ነው።

በአካዳሚክ እና በኢንዱስትሪ መካከል የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር ለመፍጠር ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነም አስረድተዋል።

ጂ.ሲ.ኤል በኢነርጂ፣ ኢንጂነሪንግ፣ በቴክኒክ፣ በትምህርት፣ በምርምርና ፈጠራ ዘርፍ ጠንካራ አቅም እንዲሁም ውጤታማ የሰው ኃይል ለማፍራት እንደ ቁልፍ ማዕከል እንደሚያገለግል አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026