🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 12/2018 (ኢዜአ)፡- የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሚያስችል የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ራቢ (ኢ/ር) ገለጹ።
የቀብሪደሃር ዩኒቨርሲቲ እና ጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ኢንቨስትመንትስ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ በኢትዮጵያ በኢነርጂ ዘርፍ የክህሎት ልማትን፣ ኢኖቬሽን እና ዘላቂ የኢነርጂ ልማትን ለማሳደግ ያለመ እንደሆነ ተመላክቷል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ስምምነቱ ለዩኒቨርሲቲው ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ አለው።
በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የንድፈ ሐሳብ ትምህርትን ከኢንዱስትሪው የተግባር ልምድ ጋር በማቀናጀት ለሀገር ግንባታ የሚሆኑ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ የሚያካሂዳቸው ጥናትና ምርምሮች ለጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ፕሮጀክቶች ግብዓት ከመሆናቸው ባሻገር ከኩባንያው የሚገኘው ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ዕውቀት ለተማሪዎችና ለሀገር የኢነርጂ ዘርፍ ትልቅ አቅም ይፈጥራልም ነው ያሉት።
ዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያን የኢነርጂ አቅም በዘላቂነት ለማልማት የሚያስችል የሰው ኃይል ማፍራት ላይ ትኩረት መስጠቱን እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል።

የጂ.ሲ.ኤል ኢነርጂ ኢንቨስትመንትስ የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ፕሬዚዳንት ሱን ዦንግ እንዳሉት፤ ስምምነቱ በቻይና እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የኢንዱስትሪ እና የትምህርት ትስስር ለማሳደግ የሚያስችል ነው።
በአካዳሚክ እና በኢንዱስትሪ መካከል የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ትብብር ለመፍጠር ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነም አስረድተዋል።
ጂ.ሲ.ኤል በኢነርጂ፣ ኢንጂነሪንግ፣ በቴክኒክ፣ በትምህርት፣ በምርምርና ፈጠራ ዘርፍ ጠንካራ አቅም እንዲሁም ውጤታማ የሰው ኃይል ለማፍራት እንደ ቁልፍ ማዕከል እንደሚያገለግል አስገንዝበዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026