የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል

Mar 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 14/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ግብርናን ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።

የግብርና ሚኒስቴር ከክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የቢሮ ኃላፊዎችና በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ከተሰማሩ ባለኃብቶች ጋር በግብርና ኢንቨስትመንት አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ነው።


የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በግብርናው ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት፣ ወጪ ምርቶችን በአይነትም በጥራትም የማሳደግ ግብ ተይዞ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።

ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን ማምረት እንዲሁም በግብርናው ዘርፍ የሥራ ዕድል ፈጠራ አቅም ማሳደግ ሌላው ግብ መሆኑንም አብራርተዋል።

ግቦቹን በውጤታማነት ለመተግበር መንግሥት የፖሊሲ እንዲሁም ስትራቴጂዎችና ሕጎች ሥራ ላይ በማዋል አስቻይ ሁኔታዎችን እየፈጠረ ይገኛል ብለዋል።

በዚህም በእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፍ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል።

የምግብ ዋስትና ማረጋገጥን ጨምሮ በግብርናው ዘርፍ የተያዙ ሀገራዊ ውጥኖችን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የግሉ ዘርፍ ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቁመው በዚህ ረገድ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።


ያለንን የግብርና አቅም አሟጦ በመጠቀም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፉን የሚያነቃቁ ልዩ ልዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆናቸውንም አመልክተዋል።

የውይይቱ ዋና ዓላማም የሰፋፊ የእርሻ ልማት አፈጻጸምን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ መሆኑን አስታውቀዋል።

ከውይይቱ ጎን ለጎን ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የታመነበት ብሄራዊ የማሽላ ፍላግሺፕ ፕሮግራም ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025