🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 14/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ግብርናን ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።
የግብርና ሚኒስቴር ከክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የቢሮ ኃላፊዎችና በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ከተሰማሩ ባለኃብቶች ጋር በግብርና ኢንቨስትመንት አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ነው።

የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በግብርናው ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት፣ ወጪ ምርቶችን በአይነትም በጥራትም የማሳደግ ግብ ተይዞ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።
ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን ማምረት እንዲሁም በግብርናው ዘርፍ የሥራ ዕድል ፈጠራ አቅም ማሳደግ ሌላው ግብ መሆኑንም አብራርተዋል።
ግቦቹን በውጤታማነት ለመተግበር መንግሥት የፖሊሲ እንዲሁም ስትራቴጂዎችና ሕጎች ሥራ ላይ በማዋል አስቻይ ሁኔታዎችን እየፈጠረ ይገኛል ብለዋል።
በዚህም በእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፍ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል።
የምግብ ዋስትና ማረጋገጥን ጨምሮ በግብርናው ዘርፍ የተያዙ ሀገራዊ ውጥኖችን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የግሉ ዘርፍ ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቁመው በዚህ ረገድ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ያለንን የግብርና አቅም አሟጦ በመጠቀም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፉን የሚያነቃቁ ልዩ ልዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆናቸውንም አመልክተዋል።
የውይይቱ ዋና ዓላማም የሰፋፊ የእርሻ ልማት አፈጻጸምን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ መሆኑን አስታውቀዋል።
ከውይይቱ ጎን ለጎን ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የታመነበት ብሄራዊ የማሽላ ፍላግሺፕ ፕሮግራም ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026