የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል

Mar 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 14/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ግብርናን ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።

የግብርና ሚኒስቴር ከክልሎችና ሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የቢሮ ኃላፊዎችና በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ከተሰማሩ ባለኃብቶች ጋር በግብርና ኢንቨስትመንት አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ነው።


የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ በግብርናው ዘርፍ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት፣ ወጪ ምርቶችን በአይነትም በጥራትም የማሳደግ ግብ ተይዞ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።

ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት የሚሆኑ ምርቶችን ማምረት እንዲሁም በግብርናው ዘርፍ የሥራ ዕድል ፈጠራ አቅም ማሳደግ ሌላው ግብ መሆኑንም አብራርተዋል።

ግቦቹን በውጤታማነት ለመተግበር መንግሥት የፖሊሲ እንዲሁም ስትራቴጂዎችና ሕጎች ሥራ ላይ በማዋል አስቻይ ሁኔታዎችን እየፈጠረ ይገኛል ብለዋል።

በዚህም በእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፍ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል።

የምግብ ዋስትና ማረጋገጥን ጨምሮ በግብርናው ዘርፍ የተያዙ ሀገራዊ ውጥኖችን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የግሉ ዘርፍ ወሳኝ ሚና እንዳለው ጠቁመው በዚህ ረገድ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።


ያለንን የግብርና አቅም አሟጦ በመጠቀም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የእርሻ ኢንቨስትመንት ዘርፉን የሚያነቃቁ ልዩ ልዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆናቸውንም አመልክተዋል።

የውይይቱ ዋና ዓላማም የሰፋፊ የእርሻ ልማት አፈጻጸምን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ መሆኑን አስታውቀዋል።

ከውይይቱ ጎን ለጎን ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የታመነበት ብሄራዊ የማሽላ ፍላግሺፕ ፕሮግራም ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026