የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የልማት ማህበሩ በተለያዩ የልማት ዘርፎች ውጤታማ ተግባር እያከናወነ ነው

Mar 26, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ):- የወላይታ ልማት ማህበር በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርናና በከተማ ልማት እንዲሁም በሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ ተግባር እያከናወነ መሆኑ ተመላከተ፡፡

የወላይታ ልማት ማህበር "ሁለንተናዊ ልማት ለህዝባችን ከፍታ" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው የገቢ ማሳባሰቢያ ፕሮግራም ተካሄዷል፡፡


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪና የወላይታ ልማት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ገብረመስቀል ጫላ እንደገለፁት፤ የልማት ማህበሩ በማህበራዊና ሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ ተግባር እያከናወነ ነው።

የልማት ማህበሩ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርናና በከተማ ልማት እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።

የልማት ማህበሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ የአውቶሞቲቭ ጋራዥን ጨምሮ 11 ፕሮጀክቶችን አስገንብቶ ወደ ስራ በማስገባት በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

በተለይ አቅመ ደካማ ወገኖችን በመርዳትና የመማር ዕድል ያልገጠማቸው ወገኖችን በማስተማር የልማት አጋርነቱን ማሳየቱን ጠቁመዋል፡፡

በዚህም በየአካባቢው ያለውን ፀጋ ወደ ልማት በመቀየር የህዝብን ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችል አቅም መፍጠር መቻሉን ጠቁመዋል፡፡

የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥም በተደራጀ መልኩ ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችለውን ስትራቴጂክ እቅድ ነድፎ ወደ ስራ መግባቱን ተናግረዋል፡፡

በዚህም ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር አጭር የጽሁፍ መልዕክትና የቴሌ ብር አካውንት አማራጭን ተግባራዊ ማድረጉን ጠቅሰዋል፡፡

በተጀመረው 650 ሚሊዮን ብር የመሰብሰብ ልዩ ዕቅድ በአጭር ጊዜ ውስጥ 50 ሚሊዮን ብር ሊሰበሰብ መቻሉንም አመልክተዋል።


የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የልማት ማህበሩ የበላይ ጠባቂ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በበኩላቸው የልማት ማህበሩ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ከመንግስት ጋር በመተባበር በርካታ የልማት ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

የተማረ የሰው ኃይልን በማፍራት ግንባር ቀደም የሆነውን ማህበር ለማጠናከር የዞኑ አስተዳደር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ልማት ማህበሩ የዞኑን ህዝብ ሁለንተናዊ ለውጥ ለማረጋገጥ በትምህርት፣ በጤና እንዲሁም በሰው ሀብት ልማት ላይ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን የገለጹት ደግሞ የልማት ማህበሩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አበባየሁ ቶራ (ዶ/ር) ናቸው።


ይህንን ተግባር በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ በተለያዩ አማራጮች የተጀመረውን የገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም አባላትና አጋሮች እንዲደግፉ ጠይቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026