🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ):- የወላይታ ልማት ማህበር በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርናና በከተማ ልማት እንዲሁም በሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ ተግባር እያከናወነ መሆኑ ተመላከተ፡፡
የወላይታ ልማት ማህበር "ሁለንተናዊ ልማት ለህዝባችን ከፍታ" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው የገቢ ማሳባሰቢያ ፕሮግራም ተካሄዷል፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪና የወላይታ ልማት ማህበር ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ገብረመስቀል ጫላ እንደገለፁት፤ የልማት ማህበሩ በማህበራዊና ሌሎች የልማት ዘርፎች ውጤታማ ተግባር እያከናወነ ነው።
የልማት ማህበሩ በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርናና በከተማ ልማት እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
የልማት ማህበሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ የአውቶሞቲቭ ጋራዥን ጨምሮ 11 ፕሮጀክቶችን አስገንብቶ ወደ ስራ በማስገባት በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።
በተለይ አቅመ ደካማ ወገኖችን በመርዳትና የመማር ዕድል ያልገጠማቸው ወገኖችን በማስተማር የልማት አጋርነቱን ማሳየቱን ጠቁመዋል፡፡
በዚህም በየአካባቢው ያለውን ፀጋ ወደ ልማት በመቀየር የህዝብን ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችል አቅም መፍጠር መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥም በተደራጀ መልኩ ገቢ ለመሰብሰብ የሚያስችለውን ስትራቴጂክ እቅድ ነድፎ ወደ ስራ መግባቱን ተናግረዋል፡፡
በዚህም ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር አጭር የጽሁፍ መልዕክትና የቴሌ ብር አካውንት አማራጭን ተግባራዊ ማድረጉን ጠቅሰዋል፡፡
በተጀመረው 650 ሚሊዮን ብር የመሰብሰብ ልዩ ዕቅድ በአጭር ጊዜ ውስጥ 50 ሚሊዮን ብር ሊሰበሰብ መቻሉንም አመልክተዋል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የልማት ማህበሩ የበላይ ጠባቂ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በበኩላቸው የልማት ማህበሩ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ከመንግስት ጋር በመተባበር በርካታ የልማት ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የተማረ የሰው ኃይልን በማፍራት ግንባር ቀደም የሆነውን ማህበር ለማጠናከር የዞኑ አስተዳደር ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ልማት ማህበሩ የዞኑን ህዝብ ሁለንተናዊ ለውጥ ለማረጋገጥ በትምህርት፣ በጤና እንዲሁም በሰው ሀብት ልማት ላይ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን የገለጹት ደግሞ የልማት ማህበሩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አበባየሁ ቶራ (ዶ/ር) ናቸው።

ይህንን ተግባር በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ በተለያዩ አማራጮች የተጀመረውን የገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም አባላትና አጋሮች እንዲደግፉ ጠይቀዋል፡፡
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026