የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ወርቃማ የቪዛ አገልግሎት የኢንቨስትመንት ዋስትናን የሚያጎናፅፍ ወሳኝ የአሰራር ሥርዓት ነው

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018(ኢዜአ)፦ ለአስር ዓመታት የሚቆየው የኢትዮጵያ ወርቃማ የቪዛ አገልግሎት ለዓለም አቀፍ አልሚዎች የኢንቨስትመንት ዋስትናን የሚያጎናፅፍ ወሳኝ የአሰራር ሥርዓት መሆኑን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ገለጸ።

የቤት ለቤት የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለመስጠትም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ጎሳ ደምሴ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ በቅድመ ሪፎርም ወቅት የፓስፖርት አገልግሎት 270 ሺህ ያልበለጠ እንደነበር አስታውሰዋል።

በአሁኑ ወቅትም የፓስፖርት፣ ጉዞና የይለፍ ሰነድ አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ቅልጥፍናን የሚያሳልጥ ስኬታማ የሪፎርም እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት እስከ 4 ሚሊየን የሚደርስ የፖስርት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል አቅም በመገንባት እየተሰራበት መሆኑን ተናግረዋል።

በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በክልል ቅርንጫፎችና ተያያዥ አማራጮችን በማስፋትም የዲጂታል ሥርዓቱን የመፈጸም አቅም ማጎልበት መቻሉን አንስተዋል።

በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የተጣለው መሰረትም በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በማጠናከር ከተቋማት ጋር የሚናበብ አስቻይ የአሰራር ምኅዳር ለመፍጠር እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቪዛ አገልግሎቶችም ምልልስን በማስቀረት በአጭር ጊዜ ውስጥ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ሁኔታ እንደተፈጠረ አስረድተዋል።

በቀጣይም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ሀገራዊ ትልም ጋር በማናበብ በኤሌክትሮኒክ፣ የኤምባሲና መዳረሻ የቪዛ አገልግሎትና መሰል ተግባራት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የፓስፖርት አገልግሎቱን ከነበረበት ኋላቀር የአሰራር በማላቀቅ 8ኛው ትውልድ የኤልክትሮኒክ ፓስፖርት ስራ ላይ ማዋል እንደተቻለ አንስተዋል።

በዚህም በነባርና አዳዲስ ቅርንጫፎች በመደበኛ የፖስፖርት አገልግሎት በ60 ቀን፣ በአስቸኳይ በሁለትና በአምስት ቀናት፤ በፕሪሚየም አገልግሎት ደግሞ በ6 ሰዓታት ውስጥ እየተሰጠ መሆኑን አስታውቀዋል።

በቀጣይም የቤት ለቤት የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ደንብ ቁጥር 587/2018 ዓ.ም የአገልግሎት ክፍያ መሠረት ለአስር ዓመት የሚቆይ የወርቃማ ቪዛ (Golden Viza) መካተቱን አስረድተዋል።

የቪዛ አገልግሎቱ አቅም ያላቸው ዓለም አቀፍ አልሚዎችን ወደ ኢትዮጵያ በመሳብ ለአስር ዓመታት ያህል በነፃነት መኖር የሚያስቻላቸውን የኢንቨስትመንት ዋስትና እንደሚያጎናጽፍ ገልጸዋል።

በርካታ ሀገራት የጎልደን ቪዛ አገልግሎት እንዳላቸው ገልጸው፤ የኢትዮጵያ ወርቃማ ቪዛም የሀገርን መገለጫዎችና የደኅንነት ጥራት በማስጠበቅ ኢንቨስትመንትን ለማስፋት አስቻይ ሁኔታን እንደሚፈጥር አንስተዋል።

በመሆኑም የቪዛ አገልግሎቱን ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቁመው፤ በአጭር ጊዜ ወደ ስራ ይገባል ብለዋል።


በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማሩ የሕንድ ባለሃብት ጋጀንድራ ሲንገህ ማንፑራ፤ የኢትዮጵያ የኢምግሬሽን አገልግሎት የዲጂታል ዘርፍ ሥር-ነቀል ለውጥ የኢንቨስትመንት መታወቂያን ያለአንዳች እንግልት ማሳደስ እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።

ሌላኛው ቻይናዊ ረሚነ ዛነግ በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ለአስር ዓመታት በሚቆየው ወርቃማ የቪዛ አገልግሎት የተረጋጋ የንግድና ኢንቨስትመንት ስራን ለመስራት ወሳኝ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል።


ወጣት መሠረት ጸጋዬ በበኩሏ፤ በኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሰጪ ሙያተኞች ሙያዊ አክብሮት ፓስፖርቷን በአጭር ጊዜ ውስጥ አሳድሳ ማጠናቀቅ እንደቻለ ገልጿለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026