የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የዲጂታል ፋይናንስ የማጭበርበር ወንጀሎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመግታት ቅንጅታዊ አሰራሮች ይጠናከራሉ

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ የማጭበርበር ወንጀሎችን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመግታት የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራሮች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የፍትህ ሚኒስትር ሃና አርአያስላሴ ገለጹ።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው እና የዲጂታል ፋይናንስ ማጭበርበርን መከላከል ላይ ትኩረት ያደረገ አውደ ጥናት እየተካሄደ ነው።


"ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ስርዓት ለሀገር ዕድገት" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ባለው አውደ ጥናት ላይ የዲጂታል ፋይናንስ ማጭበርበር በኢትዮጵያ ያለበትን ደረጃ የሚያሳይ የዳሰሳ ጥናት ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል።

የፍትህ ሚኒስትር ሃና አርአያስላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ተግባራዊ በተደረገው የዲጂታል ፋይናንስ ስርዓት በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤቶች ተገኝተዋል።


ዲጂታል ስትራቴጂ 2025ን ጨምሮ በዲጂታል 2030 ለዲጂታል ፋይናንስ ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን ገልጸው ይህም ለዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት በሚደረገው ሀገራዊ ጥረት ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም የዲጂታል ፋይናንስ ደህንነትን ለማስጠበቅና ከማጭበርበር ወንጀሎች ለመከላከል በትኩረት መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ይህንንም ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመከላከል ቅንጅታዊ አሰራሮች እንደሚጠናከሩ አመልክተው፤ የፍትህ አካላት፣ የጸጥታና ደህንነት ተቋማትን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ ነው ብለዋል።


የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በበኩላቸው፤ አውደ ጥናቱ የዲጂታል ፋይናንስ የማጭበርበር ወንጀለኞችን ለመከላከል የሚከናወኑ ተግባራትን ለማቀናጀት ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።

በአውደ ጥናቱ የጥናት ውጤቶችን መሰረት ያደረጉ የመፍትሔ ሃሳቦች ቀርበው በባለድርሻ አካላት ውይይት እንደሚደረግባቸውም ተናግረዋል።

የህግ ክፍተቶችን መለየትና የቁጥጥር ስራዎችን ማጠናከር ሌላው የአውደ ጥናቱ ዓላማ መሆኑንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025