🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ ማስፋፊያ ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ጀንበሬ እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ በዞኑ ለሚገኙ 22 የሸማች ማህበራት የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እንዲቀርብ ተደርጓል።
እስካሁን ባለው ሂደትም ከ580 ሺህ ሊትር በላይ የምግብ ዘይት፣ ከ800 ኩንታል በላይ የዳቦ ዱቄት፣ ከ4 ሺህ 500 ኩንታል በላይ ስኳር ለተጠቃሚው እንዲደርስ መደረጉን ገልጸዋል።
ጽሕፈት ቤቱ ለሚመጣው የትንሳኤ በዓል የዋጋ ንረትን ለመከላከል ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ጠቁመው በዚህም ከ20 ሺህ ኩንታል በላይ ጤፍ፣ የዳቦ ዱቄት፣ ስኳርና ሽንኩርት በህብረት ስራ አማካኝነት ለገበያ ለማቅረብ እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026