🔇Unmute
ባሕርዳር፤ መጋቢት 22/2018(ኢዜአ)፦ በክልሉ በቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ እርካታን ከፍ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ገለፀ።
የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አጋር ተቋማትን ያሳተፈ ወርክ ሾፕ በባህር ዳር ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ የቻለ ይግዛው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ የሚያደርጉ ቴክኖሎጂዎች ለምተው በተቋማት ተግባራዊ እንዲሆኑ ተደርጓል።

የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር፣ በመፍጠር፣ በማልማትና በማሻሻል ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ስራዎች የማዋል ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልፀዋል።
በአሁኑ ወቅት የግብርናውን ምርታማነት ለማሳደግ፣ የማዕድንና የቱሪዝም ብሎም ሌሎች የአገልግሎት ዘርፎችን ማዘመን የሚያስችሉ አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ማቅረብ እየተቻለ ነው ብለዋል።
የዛሬው መድረክም የከፍተኛ ትምህርት እና የሌሎች ተቋማት ትስስርን የማጠናከር ዓላማ ያለው መሆኑንም አስረድተዋል።
የአማራ ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ልማትን ለማረጋገጥ ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎች በብዛትም ሆነ በጥራት መጠቀም ይገባል።
በተለይም የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚን እውን በማድረግ፣ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራ በትኩረት እየተከናወነ እንደሆነ ገልፀዋል።

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት መንገሻ አየን(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ልማት ዘርፋን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት።
በዚህም የክልሉን የገቢ አሰባሰብ ያዘመነ ውጤታማ ቴክኖሎጂ ለምቶ ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን ብቃት ያላቸው ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመጠቀም በትብብር የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025
ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...
Feb 24, 2025