የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮችን ተደራሽ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ እርካታን ለማሳደግ እየተሰራ ነው

Apr 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕርዳር፤ መጋቢት 22/2018(ኢዜአ)፦ በክልሉ በቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ እርካታን ከፍ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ገለፀ።

የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አጋር ተቋማትን ያሳተፈ ወርክ ሾፕ በባህር ዳር ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ የቻለ ይግዛው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ የሚያደርጉ ቴክኖሎጂዎች ለምተው በተቋማት ተግባራዊ እንዲሆኑ ተደርጓል።


የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር፣ በመፍጠር፣ በማልማትና በማሻሻል ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ስራዎች የማዋል ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልፀዋል።

በአሁኑ ወቅት የግብርናውን ምርታማነት ለማሳደግ፣ የማዕድንና የቱሪዝም ብሎም ሌሎች የአገልግሎት ዘርፎችን ማዘመን የሚያስችሉ አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ማቅረብ እየተቻለ ነው ብለዋል።

የዛሬው መድረክም የከፍተኛ ትምህርት እና የሌሎች ተቋማት ትስስርን የማጠናከር ዓላማ ያለው መሆኑንም አስረድተዋል።

የአማራ ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ልማትን ለማረጋገጥ ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎች በብዛትም ሆነ በጥራት መጠቀም ይገባል።

በተለይም የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚን እውን በማድረግ፣ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራ በትኩረት እየተከናወነ እንደሆነ ገልፀዋል።


የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት መንገሻ አየን(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ልማት ዘርፋን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት።

በዚህም የክልሉን የገቢ አሰባሰብ ያዘመነ ውጤታማ ቴክኖሎጂ ለምቶ ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን ብቃት ያላቸው ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመጠቀም በትብብር የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026