የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮችን ተደራሽ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ እርካታን ለማሳደግ እየተሰራ ነው

Apr 1, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕርዳር፤ መጋቢት 22/2018(ኢዜአ)፦ በክልሉ በቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ እርካታን ከፍ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ገለፀ።

የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አጋር ተቋማትን ያሳተፈ ወርክ ሾፕ በባህር ዳር ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ የቻለ ይግዛው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ የሚያደርጉ ቴክኖሎጂዎች ለምተው በተቋማት ተግባራዊ እንዲሆኑ ተደርጓል።


የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን በምርምር፣ በመፍጠር፣ በማልማትና በማሻሻል ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማት ስራዎች የማዋል ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልፀዋል።

በአሁኑ ወቅት የግብርናውን ምርታማነት ለማሳደግ፣ የማዕድንና የቱሪዝም ብሎም ሌሎች የአገልግሎት ዘርፎችን ማዘመን የሚያስችሉ አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን ማቅረብ እየተቻለ ነው ብለዋል።

የዛሬው መድረክም የከፍተኛ ትምህርት እና የሌሎች ተቋማት ትስስርን የማጠናከር ዓላማ ያለው መሆኑንም አስረድተዋል።

የአማራ ክልል ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ልማትን ለማረጋገጥ ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎች በብዛትም ሆነ በጥራት መጠቀም ይገባል።

በተለይም የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚን እውን በማድረግ፣ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራ በትኩረት እየተከናወነ እንደሆነ ገልፀዋል።


የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት መንገሻ አየን(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ልማት ዘርፋን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት።

በዚህም የክልሉን የገቢ አሰባሰብ ያዘመነ ውጤታማ ቴክኖሎጂ ለምቶ ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን ብቃት ያላቸው ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና በመጠቀም በትብብር የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026