🔇Unmute
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አዲስ የልማት ምዕራፍ መክፈቱን የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ።
በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተመዘገቡ ስኬቶች ከአሥር ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣሙ ናቸው
የገንዘብ ሚኒስቴር ባለፉት 18 ወራት የተከናወኑ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ እና መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ውጤታማነት የሚገመግም ዝርዝር ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

በሪፖርቱ መሠረት የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተወሰዱ እርምጃዎች ውጤት እያሳዩ መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን የወጪ ንግድ ገቢ በማሳደግ ረገድ እንዲሁም በሌሎችም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተመዝግበዋል።
የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ማሻሻያው በኢትዮጵያ አዲስ የልማት ምዕራፍ የከፈተና ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡበት መሆኑን ገልጸዋል።
ሪፖርቱ በኢኮኖሚ ማኔጅመንት ቡድን አማካኝነት በራስ አቅም የተዘጋጀ መሆኑ በአሁኑ ወቅት በተቋማት ውስጥ ጠንካራ አቅም ያላቸው ባለሙያዎች እየተፈጠሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የመንግሥት ተቋማት የፖሊሲ ነጻነት ያላቸው መሆኑ ለማሻሻያው ስኬታማነት ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቁመዋል።
ብሔራዊ ባንክ ትልቅ እመርታ እና የፋይናንስ ሥርዓቱን ጤናማነት ለማረጋገጥ አመርቂ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ባንኩ የዋጋ ማረጋጋት እና የፋይናንሻል ዘርፉን ጤነኛነት ለመጠበቅ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ሪፖርቱ እስካሁን የተመዘገቡ ስኬቶችን ብቻ ሳይሆን፣ በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራትንም በዝርዝር ማካተቱን ጠቅሰዋል።
የአምራች ሴክተሩ እንዲነቃቃ እና ለሀገር ኢኮኖሚ የሚጠበቀውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የሀገር በቀል ሪፎርሙ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልፀው፥ ሪፖርቱ የኢትዮጵያን ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትክክለኛ አቅጣጫ የሚያሳይ መሆኑን አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026