የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አዲስ የልማት ምዕራፍ ከፍቷል

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አዲስ የልማት ምዕራፍ መክፈቱን የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ።

በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተመዘገቡ ስኬቶች ከአሥር ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣሙ ናቸው

የገንዘብ ሚኒስቴር ባለፉት 18 ወራት የተከናወኑ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ እና መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ውጤታማነት የሚገመግም ዝርዝር ሪፖርት ይፋ አድርጓል።


በሪፖርቱ መሠረት የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተወሰዱ እርምጃዎች ውጤት እያሳዩ መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን የወጪ ንግድ ገቢ በማሳደግ ረገድ እንዲሁም በሌሎችም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተመዝግበዋል።

የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ማሻሻያው በኢትዮጵያ አዲስ የልማት ምዕራፍ የከፈተና ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡበት መሆኑን ገልጸዋል።

ሪፖርቱ በኢኮኖሚ ማኔጅመንት ቡድን አማካኝነት በራስ አቅም የተዘጋጀ መሆኑ በአሁኑ ወቅት በተቋማት ውስጥ ጠንካራ አቅም ያላቸው ባለሙያዎች እየተፈጠሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት የመንግሥት ተቋማት የፖሊሲ ነጻነት ያላቸው መሆኑ ለማሻሻያው ስኬታማነት ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቁመዋል።

ብሔራዊ ባንክ ትልቅ እመርታ እና የፋይናንስ ሥርዓቱን ጤናማነት ለማረጋገጥ አመርቂ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ባንኩ የዋጋ ማረጋጋት እና የፋይናንሻል ዘርፉን ጤነኛነት ለመጠበቅ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ሪፖርቱ እስካሁን የተመዘገቡ ስኬቶችን ብቻ ሳይሆን፣ በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራትንም በዝርዝር ማካተቱን ጠቅሰዋል።

የአምራች ሴክተሩ እንዲነቃቃ እና ለሀገር ኢኮኖሚ የሚጠበቀውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የሀገር በቀል ሪፎርሙ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልፀው፥ ሪፖርቱ የኢትዮጵያን ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትክክለኛ አቅጣጫ የሚያሳይ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026