🔇Unmute
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አዲስ የልማት ምዕራፍ መክፈቱን የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ገለጹ።
በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተመዘገቡ ስኬቶች ከአሥር ዓመቱ የልማት ዕቅድ ጋር የተጣጣሙ ናቸው
የገንዘብ ሚኒስቴር ባለፉት 18 ወራት የተከናወኑ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ እና መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን ውጤታማነት የሚገመግም ዝርዝር ሪፖርት ይፋ አድርጓል።

በሪፖርቱ መሠረት የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የተወሰዱ እርምጃዎች ውጤት እያሳዩ መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን የወጪ ንግድ ገቢ በማሳደግ ረገድ እንዲሁም በሌሎችም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተመዝግበዋል።
የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ማሻሻያው በኢትዮጵያ አዲስ የልማት ምዕራፍ የከፈተና ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡበት መሆኑን ገልጸዋል።
ሪፖርቱ በኢኮኖሚ ማኔጅመንት ቡድን አማካኝነት በራስ አቅም የተዘጋጀ መሆኑ በአሁኑ ወቅት በተቋማት ውስጥ ጠንካራ አቅም ያላቸው ባለሙያዎች እየተፈጠሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የመንግሥት ተቋማት የፖሊሲ ነጻነት ያላቸው መሆኑ ለማሻሻያው ስኬታማነት ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቁመዋል።
ብሔራዊ ባንክ ትልቅ እመርታ እና የፋይናንስ ሥርዓቱን ጤናማነት ለማረጋገጥ አመርቂ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ባንኩ የዋጋ ማረጋጋት እና የፋይናንሻል ዘርፉን ጤነኛነት ለመጠበቅ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ሪፖርቱ እስካሁን የተመዘገቡ ስኬቶችን ብቻ ሳይሆን፣ በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራትንም በዝርዝር ማካተቱን ጠቅሰዋል።
የአምራች ሴክተሩ እንዲነቃቃ እና ለሀገር ኢኮኖሚ የሚጠበቀውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የሀገር በቀል ሪፎርሙ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ገልፀው፥ ሪፖርቱ የኢትዮጵያን ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትክክለኛ አቅጣጫ የሚያሳይ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026