የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡

በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ መንግስቱ ሂርባዬ በዞኑ በበልግ አዝመራ 294 ሺህ 389 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ዕቅድ ተይዟል ብለዋል።

እስካሁን በተካሄደው ስራም 260 ሺህ 780 ሄክታር መሬት በአራት ዋና ዋና ሰብሎች በዘር መሸፈኑን ገልጸዋል፡፡


የተጠቀሰው ሄክታር መሬትም በበቆሎ፣ በስንዴ፣ በጤፍ፣ በቦሎቄና በሌሎች ሰብል ዘር መሸፈኑን ገልጸው የግብርና ስራውን ለማሳካትም የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ አቅርቦቱም በወቅቱ ለአርሶ አደሩ መድረሱን ጠቁመዋል።

በዘር ከተሸፈነው መሬትም እስካሁን 239 ሺህ 230 ሄክታር በመስመር፣ 175 ሺህ 209 ሄክታሩ ደግሞ በኩታ ገጠም የእርሻ ስነ-ዘዴ መልማቱን አስታውቀዋል፡፡

በዞኑ ቆላማ አካባቢ የዝናቡ ስርጭት የሚቆየው ለተወሰነ ጊዜ በመሆኑ የዘር ስራውን ለማፋጠን በርካታ ትራክተሮች መሰማራታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በበልግ አዝመራ ልማቱ ከ95 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች መሳተፋቸውን ተናግረዋል፡፡

ምርታማነቱን ለማሳደግም ከ95 ሺህ 403 ኩንታል በላይ ማዳበሪያና 42 ሺህ 262 ኩንታል የምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩና ለአርብቶ አደሩ መከፋፈሉንም አብራርተዋል፡፡

በዞኑ በበልግ አዝመራ ከሚለማው መሬትም ከ7 ሚሊዮን 175 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል፡፡


በዞኑ አዶላ ወረዳ የሞኤ ቦኮ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ሹና ጎበና ለበልግ አዝመራ ያዘጋጁትን መሬት በዘር በመሸፈን ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ምርታማነታቸውንም ለማሳደግ የአፈር ማዳበሪያ ምርጥ ዘር መጠቀማቸውን ተናግረዋል፡፡

በዞኑ ያለው ደጋ፣ ወይና ደጋና ቆላማ የአየር ጸባይ ለሰብል ልማትና ለእንስሳት እርባታ አመቺ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026