🔇Unmute
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ መንግስቱ ሂርባዬ በዞኑ በበልግ አዝመራ 294 ሺህ 389 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ዕቅድ ተይዟል ብለዋል።
እስካሁን በተካሄደው ስራም 260 ሺህ 780 ሄክታር መሬት በአራት ዋና ዋና ሰብሎች በዘር መሸፈኑን ገልጸዋል፡፡

የተጠቀሰው ሄክታር መሬትም በበቆሎ፣ በስንዴ፣ በጤፍ፣ በቦሎቄና በሌሎች ሰብል ዘር መሸፈኑን ገልጸው የግብርና ስራውን ለማሳካትም የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ አቅርቦቱም በወቅቱ ለአርሶ አደሩ መድረሱን ጠቁመዋል።
በዘር ከተሸፈነው መሬትም እስካሁን 239 ሺህ 230 ሄክታር በመስመር፣ 175 ሺህ 209 ሄክታሩ ደግሞ በኩታ ገጠም የእርሻ ስነ-ዘዴ መልማቱን አስታውቀዋል፡፡
በዞኑ ቆላማ አካባቢ የዝናቡ ስርጭት የሚቆየው ለተወሰነ ጊዜ በመሆኑ የዘር ስራውን ለማፋጠን በርካታ ትራክተሮች መሰማራታቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በበልግ አዝመራ ልማቱ ከ95 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች መሳተፋቸውን ተናግረዋል፡፡
ምርታማነቱን ለማሳደግም ከ95 ሺህ 403 ኩንታል በላይ ማዳበሪያና 42 ሺህ 262 ኩንታል የምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩና ለአርብቶ አደሩ መከፋፈሉንም አብራርተዋል፡፡
በዞኑ በበልግ አዝመራ ከሚለማው መሬትም ከ7 ሚሊዮን 175 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል፡፡

በዞኑ አዶላ ወረዳ የሞኤ ቦኮ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ሹና ጎበና ለበልግ አዝመራ ያዘጋጁትን መሬት በዘር በመሸፈን ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ምርታማነታቸውንም ለማሳደግ የአፈር ማዳበሪያ ምርጥ ዘር መጠቀማቸውን ተናግረዋል፡፡
በዞኑ ያለው ደጋ፣ ወይና ደጋና ቆላማ የአየር ጸባይ ለሰብል ልማትና ለእንስሳት እርባታ አመቺ መሆኑ ይታወቃል፡፡
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026