🔇Unmute
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፦በጅግጅጋ ከተማ ለበዓል ገበያ በቂ የእርድ እንስሳትና የግብርና ምርቶች አቅርቦት መኖሩን ሸማቾችና ነጋዴዎች ገለጹ።
በጅግጅጋ ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው ነጋዴዎችና ሸማቾች ለዘንድሮው የትንሣዔ በዓል በከተማዋ በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች የፍጆታ ምርቶች አቅርቦትና ግብይት መኖሩን ገልጸዋል።
ወይዘሮ ሲሃም በድሪ በአትክልት ምርቶች ንግድ ላይ የተሠማሩ ሲሆኑ በበዓል ገበያው በቂ ምርት መኖሩን በመግለፅ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።

በምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ አለመታየቱን እና በአሁን ወቅት በምርት አቅርቦት በኩል ችግር አለመኖሩን ገልጸዋል።
ከፍየል ነጋዴዎች መካከል ወይዘሮ አሚና ዩሱፍ በገበያው በቂ የእርድ እንስሳት መቅረቡን ተናግረዋል።
በእንቁላል ምርት ሽያጭ ላይ የተሠማሩት አቶ ታረቀኝ ጀምበሩ በበኩላቸው ለበዓሉ በቂ ምርት መኖሩን ጠቅሰዋል።
የጅግጅጋ ከተማ ንግድና ገበያ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ ለይላ መሀመድ በበኩላቸው፤ ለትንሳኤ የበዓል ገበያ የግብርናና የፋብሪካ ምርቶች እጥረት እንዳይፈጠር ከህብረት ስራ ማህበራት ጋር በቅንጅት መሰራቱን አንስተዋል።
የበዓል ምርቶቹን በበቂ ሁኔታ ከማቅረብ ባለፈ ህገ ወጥ ንግድን ለመቆጣጠር ክትትል እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026