የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በጅግጅጋ ከተማ ለበዓል ገበያ የእርድ እንስሳትና የፍጆታ ምርት በበቂ ሁኔታ ቀርቧል

Apr 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 1/2018 (ኢዜአ)፦በጅግጅጋ ከተማ ለበዓል ገበያ በቂ የእርድ እንስሳትና የግብርና ምርቶች አቅርቦት መኖሩን ሸማቾችና ነጋዴዎች ገለጹ።

በጅግጅጋ ከተማ ኢዜአ ያነጋገራቸው ነጋዴዎችና ሸማቾች ለዘንድሮው የትንሣዔ በዓል በከተማዋ በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች የፍጆታ ምርቶች አቅርቦትና ግብይት መኖሩን ገልጸዋል።

ወይዘሮ ሲሃም በድሪ በአትክልት ምርቶች ንግድ ላይ የተሠማሩ ሲሆኑ በበዓል ገበያው በቂ ምርት መኖሩን በመግለፅ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እያቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል።


በምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ አለመታየቱን እና በአሁን ወቅት በምርት አቅርቦት በኩል ችግር አለመኖሩን ገልጸዋል።

ከፍየል ነጋዴዎች መካከል ወይዘሮ አሚና ዩሱፍ በገበያው በቂ የእርድ እንስሳት መቅረቡን ተናግረዋል።

በእንቁላል ምርት ሽያጭ ላይ የተሠማሩት አቶ ታረቀኝ ጀምበሩ በበኩላቸው ለበዓሉ በቂ ምርት መኖሩን ጠቅሰዋል።

የጅግጅጋ ከተማ ንግድና ገበያ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ ለይላ መሀመድ በበኩላቸው፤ ለትንሳኤ የበዓል ገበያ የግብርናና የፋብሪካ ምርቶች እጥረት እንዳይፈጠር ከህብረት ስራ ማህበራት ጋር በቅንጅት መሰራቱን አንስተዋል።

የበዓል ምርቶቹን በበቂ ሁኔታ ከማቅረብ ባለፈ ህገ ወጥ ንግድን ለመቆጣጠር ክትትል እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026