የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከተሞችን ወደ አምራችነት እያሸጋገረ ነው   

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ሚያዚያ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የተተገበረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከተሞችን ወደ አምራችነት እያሸጋገረ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በተለይም በእንስሳት ሀብት ልማት የተከናወኑ ተግባራት ነዋሪውን ከሸማችነት ወደ አምራችነት ከማሸጋገር ባለፈ ለትንሳኤ በዓል የተሻለ አቅርቦት እንዲኖር እድል ፈጥሯል ብለዋል።

ቢሮው የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርት አቅርቦት ዙሪያ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

የቢሮ ሃላፊው ጋሻው ሙጨ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሌማት ትሩፋት ከመተግበሩ በፊት ከተሞች ከገጠር የሚመጣው ምርት ተጠቃሚ እንጂ አምራች አልነበሩም።

ይህንን ልምድ ለመቀየር በተለይም አካባቢን መሰረት ያደረገ የእንስሳት ልማት ስራ በልዩ ትኩረት ሲከናወን መቆየቱን ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳደሮች ወጣቶችን በማደራጀት፣ ባለሀብቶችንና ግለሰቦችን በማሳተፍ በእንስሳት ማድለብ፣ በዶሮና በወተት ልማት በማሰማራታቸው ከተሞች አሁን ላይ የራሳቸውን ምርት ማመንጨት ወደሚችሉበት ደረጃ ደርሰዋል ብለዋል።

በከተማና በገጠር በተከናወነ የተቀናጀ ስራ ለዘንድሮው የትንሳኤ በዓል ገበያ በተሻለ መልኩ የእርድ እንስሳት፣ የዶሮ፣ የእንቁላልና የወተት ምርቶች በተዘጋጁ ማዕከላት ለህብረተሰቡ እየቀረቡ ይገኛሉ ነው ያሉት።

የወተት ምርትም ከክልሉ አልፎ ወደ አዲስ አበባና አጎራባች ክልሎች በስፋት እየቀረበ መሆኑን አስረድተዋል።

የከተማ አስተዳደሮች ለወጣቶች ቦታና ብድር በማመቻቸት፣ የእንስሳት ሀብት ልማቱ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ታግዞ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026