የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከተሞችን ወደ አምራችነት እያሸጋገረ ነው   

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ሚያዚያ 2/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የተተገበረው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከተሞችን ወደ አምራችነት እያሸጋገረ መሆኑን የክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በተለይም በእንስሳት ሀብት ልማት የተከናወኑ ተግባራት ነዋሪውን ከሸማችነት ወደ አምራችነት ከማሸጋገር ባለፈ ለትንሳኤ በዓል የተሻለ አቅርቦት እንዲኖር እድል ፈጥሯል ብለዋል።

ቢሮው የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርት አቅርቦት ዙሪያ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

የቢሮ ሃላፊው ጋሻው ሙጨ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የሌማት ትሩፋት ከመተግበሩ በፊት ከተሞች ከገጠር የሚመጣው ምርት ተጠቃሚ እንጂ አምራች አልነበሩም።

ይህንን ልምድ ለመቀየር በተለይም አካባቢን መሰረት ያደረገ የእንስሳት ልማት ስራ በልዩ ትኩረት ሲከናወን መቆየቱን ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳደሮች ወጣቶችን በማደራጀት፣ ባለሀብቶችንና ግለሰቦችን በማሳተፍ በእንስሳት ማድለብ፣ በዶሮና በወተት ልማት በማሰማራታቸው ከተሞች አሁን ላይ የራሳቸውን ምርት ማመንጨት ወደሚችሉበት ደረጃ ደርሰዋል ብለዋል።

በከተማና በገጠር በተከናወነ የተቀናጀ ስራ ለዘንድሮው የትንሳኤ በዓል ገበያ በተሻለ መልኩ የእርድ እንስሳት፣ የዶሮ፣ የእንቁላልና የወተት ምርቶች በተዘጋጁ ማዕከላት ለህብረተሰቡ እየቀረቡ ይገኛሉ ነው ያሉት።

የወተት ምርትም ከክልሉ አልፎ ወደ አዲስ አበባና አጎራባች ክልሎች በስፋት እየቀረበ መሆኑን አስረድተዋል።

የከተማ አስተዳደሮች ለወጣቶች ቦታና ብድር በማመቻቸት፣ የእንስሳት ሀብት ልማቱ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ታግዞ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆን ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026