የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በአምራች ኢንዱስትሪዎች ለተኪና ወጪ ንግድ ምርቶች እድገት ትኩረት ተሰጥቶ ተከናውኗል

Apr 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህርዳር፤ ሚያዚያ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በአምራች ኢንዱስትሪዎች ለተኪና ወጪ ንግድ የሚውሉ ምርቶችን በዓይነትና በብዛት የማምረት ስራ ትኩረት ተሰጥቶት መከናወኑን የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።

መንግስት የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ተግባራዊ በማድረግ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ያለውን ችግር በጋራ በመፍታት ዘላቂነት ያለው እድገትና ተወዳዳሪነት እንዲመዘገብ እያደረገ ይገኛል።

በዚህም በርካታ ኢንዱስትሪዎች የመሰረተ ልማትና ሌሎች ችግሮቻቸው እየተፈታ የማምረት አቅማቸው እየጎለበተ ውጤታማ በመሆን ላይ ናቸው።


ኢንዱስትሪዎች ወጪ ምርቶችን እንዲሁም ተኪ ምርቶችን በራስ አቅም በማምረት የውጭ ምንዛሬ እጥረትን በማቃለል ለሀገር እድገት ያላቸው አስተዋጽኦ እየጨመረ የመጣበት ሁኔታ እየተፈጠረ ይገኛል ።

‎ከዚሁ ጋር ተያይዞ የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅንቄ በመታገዝ የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም እንዲጎለብት ተደርጓል።

በወራቶቹ በንቅናቄው በተደረገ ጥረት 137 ከፍተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የውሃ፣ የመብራትና የመንገድ መሰረተ ልማቶች ተሟልተውላቸው ወደ ማምረት ሥራ ተሸጋግረዋል።


በአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና የኤክስፖርት ምርቶችን በዓይነትና በብዛት በማምረት ለሀገር እድገት ጥቅም ላይ ለማዋል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

‎በዚህም ከ554 ሺህ ቶን በላይ ተኪ ምርት በማምረት መንግስት ሊያወጣ የነበረውን 650 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል ብለዋል።

‎እንዲሁም በአምራች ኢንዱስትሪዎች የተመረተ 123 ሺህ ቶን ምርት ለውጭ ገበያ መቅረቡን ጠቅሰዋል።

‎በተጨማሪም ከ306 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ከ2ሺህ 925 በላይ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች ፈቃድ ወስደው ወደ ተግባር እንዲገቡ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

‎ፈቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ማምረት ሲሸጋገሩ ከ450 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩም አመላክተዋል።

‎በተቋሙ ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመተግበር የአገልግሎት አሰጣጡን ግልጽ፣ ፍትሃዊ፣ ምቹና ተጠያቂነት ያለው ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

‎በቀጣይም ቢሮው አምራች ኢንዱስትሪዎችን በልዩ ሁኔታ በመደገፍ ፈጥነው ወደ ማምረት ሥራ እንዲሸጋገሩና ወደምርት የገቡትም ምርታቸውን እንዲያሳድጉ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026