የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በሐረሪ ክልል በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር አበረታች ውጤት ተመዝግቧል

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር ፤ ሚያዝያ 06/2018 (ኢዜአ) ፦ በሐረሪ ክልል እየተከናወነ ባለው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የእንሰሳት ሃብት ልማት ዳይሬክተር ናኦል አብዱማሊክ ለኢዜአ እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር በተከናወኑ ተግባራት በእንስሳት ሀብት ልማትና ምርታማነት ላይ አበረታች ውጤት ተመዝግቧል።


በዚህም የወተት ምርትን በማሳደግ፣ የእንቁላልና የማር ምርት አቅርቦትን በማሻሻል ረገድ ተጨባጭ ውጤት መታየቱን ጠቁመዋል።

የክልሉ መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብርን ማበረታታቱን አንስተው፤ በበጀት ዓመቱ ባለፉት 9 ወራትም 12 ሼዶችን በከተማና በገጠር በመገንባት ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል።

እንዲሁም የእንስሳት መኖ አቅርቦትን የማጎልበት ተግባራት መከናወኑንም አብራርተዋል።

በዶሮ እርባታም በበጀት ዓመቱ 12ሺህ የዶሮ ጫጩቶችን ለህብረተሰቡ የማሰራጨት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም የህብረተሰቡ ፍላጎት እያደገ በመምጣቱ በራቱ ተነሳሽነት ግዢ እየፈጸመ መሆኑን አስረድተዋል።

ምርቱም በከተማው የቅዳሜና እሁድ ገበያ በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት እየቀረበ እንደሚገኝም አስረድተዋል።

በክልሉ በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የተለያዩ ዘርፎች ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ በዘርፉ የተሰማሩ አርሶ አደሮችና ሌሎች ግለሰቦች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በዘርፉ ለወጣቶች የስራ እድል ከመፈጠሩ ባለፈ ገበያን በማረጋጋት ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026