🔇Unmute
ሐረር ፤ ሚያዝያ 06/2018 (ኢዜአ) ፦ በሐረሪ ክልል እየተከናወነ ባለው የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር አበረታች ውጤት መመዝገቡን የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የእንሰሳት ሃብት ልማት ዳይሬክተር ናኦል አብዱማሊክ ለኢዜአ እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር በተከናወኑ ተግባራት በእንስሳት ሀብት ልማትና ምርታማነት ላይ አበረታች ውጤት ተመዝግቧል።

በዚህም የወተት ምርትን በማሳደግ፣ የእንቁላልና የማር ምርት አቅርቦትን በማሻሻል ረገድ ተጨባጭ ውጤት መታየቱን ጠቁመዋል።
የክልሉ መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብርን ማበረታታቱን አንስተው፤ በበጀት ዓመቱ ባለፉት 9 ወራትም 12 ሼዶችን በከተማና በገጠር በመገንባት ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል።
እንዲሁም የእንስሳት መኖ አቅርቦትን የማጎልበት ተግባራት መከናወኑንም አብራርተዋል።
በዶሮ እርባታም በበጀት ዓመቱ 12ሺህ የዶሮ ጫጩቶችን ለህብረተሰቡ የማሰራጨት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህም የህብረተሰቡ ፍላጎት እያደገ በመምጣቱ በራቱ ተነሳሽነት ግዢ እየፈጸመ መሆኑን አስረድተዋል።
ምርቱም በከተማው የቅዳሜና እሁድ ገበያ በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት እየቀረበ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
በክልሉ በሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብር የተለያዩ ዘርፎች ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ በዘርፉ የተሰማሩ አርሶ አደሮችና ሌሎች ግለሰቦች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ገልጸዋል።
በተለይም በዘርፉ ለወጣቶች የስራ እድል ከመፈጠሩ ባለፈ ገበያን በማረጋጋት ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026