የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በዞኑ በበልግ ወቅቱ ከ92 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ዘር ተሸፍኗል

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሚያዚያ 6/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን እየጣለ ያለውን የበልግ ወቅት ዝናብ በመጠቀም ከ92 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡

በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው።

በዚህም በበልግ ወቅቱ ከ104 ሺህ 600 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

እስካሁን በተደረገ ጥረት ከ92 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ዘር መሸፈኑን ጠቁመው ከተዘራው ውስጥ ስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍ፣ ቦለቄ፣ ማሾ፣አተር፣ ምስርና ሌሎች ሰብሎች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

እቅዱን ለማሳካትም እስከ ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ፈጥነው የሚደርሱ ሰብሎች ላይ በማተኮር የዘር ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አስገንዝበዋል።

በቀጣይም አርሶ አደሩ የሰብሉን ሁኔታ በመከታተል የአረምና የተባይ ቁጥጥር ስራ እንዲያከናውን የባለሙያ ድጋፍ እንደሚደረግ አመላክተዋል።

የበልግ ልማቱን ምርታማነት ለማሳደግም ለአርሶ አደሩ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ቀድሞ መቅረቡን ተናግረዋል።

በዞኑ ተሁለደሬ ወረዳ የቀበሌ 01 ነዋሪ አርሶ አደር አህመድ መሀመድ በበኩላቸው፣ የዘንድሮው የበልግ ዝናብ ለሰብል ልማት ምቹ በመሆኑ አንድ ሄክታር ተኩል ማሳቸውን በስንዴና በጤፍ ማልማታቸውን ጠቁመዋል።

ለስራው ስኬትም የግብርና ግብዓት በወቅቱ ማግኘታቸውን ጠቁመው ሰብሉን በተገቢው በመንከባከብ ጥሩ ምርት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።

እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም አንድ ሄክታር ማሳቸውን በስንዴና ገብስ ዘር መሸፈናቸውን የተናገሩት ደግሞ በኩታበር ወረዳ የቀበሌ 03 ነዋሪ አርሶ አደር ይመር ሰይድ ናቸው።

የሰብሉ ቡቃያ ያማረ በመሆኑ ከአረምና ከተባይ የመጠበቅ ስራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026