የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በዞኑ በበልግ ወቅቱ ከ92 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ዘር ተሸፍኗል

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሚያዚያ 6/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን እየጣለ ያለውን የበልግ ወቅት ዝናብ በመጠቀም ከ92 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡

በመምሪያው የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ነው።

በዚህም በበልግ ወቅቱ ከ104 ሺህ 600 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

እስካሁን በተደረገ ጥረት ከ92 ሺህ 400 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ዘር መሸፈኑን ጠቁመው ከተዘራው ውስጥ ስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍ፣ ቦለቄ፣ ማሾ፣አተር፣ ምስርና ሌሎች ሰብሎች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

እቅዱን ለማሳካትም እስከ ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ፈጥነው የሚደርሱ ሰብሎች ላይ በማተኮር የዘር ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አስገንዝበዋል።

በቀጣይም አርሶ አደሩ የሰብሉን ሁኔታ በመከታተል የአረምና የተባይ ቁጥጥር ስራ እንዲያከናውን የባለሙያ ድጋፍ እንደሚደረግ አመላክተዋል።

የበልግ ልማቱን ምርታማነት ለማሳደግም ለአርሶ አደሩ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ቀድሞ መቅረቡን ተናግረዋል።

በዞኑ ተሁለደሬ ወረዳ የቀበሌ 01 ነዋሪ አርሶ አደር አህመድ መሀመድ በበኩላቸው፣ የዘንድሮው የበልግ ዝናብ ለሰብል ልማት ምቹ በመሆኑ አንድ ሄክታር ተኩል ማሳቸውን በስንዴና በጤፍ ማልማታቸውን ጠቁመዋል።

ለስራው ስኬትም የግብርና ግብዓት በወቅቱ ማግኘታቸውን ጠቁመው ሰብሉን በተገቢው በመንከባከብ ጥሩ ምርት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።

እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም አንድ ሄክታር ማሳቸውን በስንዴና ገብስ ዘር መሸፈናቸውን የተናገሩት ደግሞ በኩታበር ወረዳ የቀበሌ 03 ነዋሪ አርሶ አደር ይመር ሰይድ ናቸው።

የሰብሉ ቡቃያ ያማረ በመሆኑ ከአረምና ከተባይ የመጠበቅ ስራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026