🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ የከተማ እና ከተሜነት እሳቤ ለሀገር ግንባታ ቁልፍ ሚና እንዳለው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
“የሉዓላዊነት ልብ” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቆይታቸው የከተማ እና የከተሜነት እሳቤ ለሀገረ መንግስት ግንባታ ስኬት ያለውን ወሳኝ ሚና አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል።
በገለጻቸውም የሀገረ መንግስት ግንባታ ሊከናወንና ሊሳካ የሚችለው በጥግግት የሚኖሩ ሰዎች ሲኖሩ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በጥግግት የሚኖር ማህበረሰብ ለኢኖቬሽን እና ለውድድር እጅግ ወሳኝ መሆኑንም አብራርተዋል።
የሕዝብ ጥግግት ለልማት እጅግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ልማትንና ብልጽግናን የሚያስብ ማንኛውም መንግስት ከተማን፣ ከተሜነትን፣ ግብር መክፈልንና አገልግሎት መስጠትን ማዕከሉ ካላደረገ ልማት ሊያመጣ እንደማይችል አስገንዝበዋል።
ከተማ አያስፈልግኝም፣ የእኔ ትኩረት አርሶ አደር ብቻ ነው የሚል እሳቤ ካለ ልማትን ማሰብ እንደማይቻልም አክለው ገልጸዋል።
በጥግግት የሚኖር ማህበረሰብ የመፍጠር አቅሙ ከፍተኛና የነቃ መሆኑን ገልጸው ማህበረሰቡ ግብር የሚከፍልና ለመሠረተ ልማት ቅርብ በመሆኑ የሚነገረውን በቅርበት እንደሚሰማም አስረድተዋል።
መንግስት ከትናንትናው ጠቃሚ የሆኑ ጉዳዮችን በመውሰድ ቀጣይነትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት ማድረጉን ገልጸዋል።
ባለፉት ጊዜያት የነበሩ ስራዎች እየታረሙና እየታረቁ በመሄዳቸውም በአሁኑ ወቅት አመርቂ ውጤት እየመጣ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026