🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦የቅርስ ልማት እና ጥበቃ ስራ ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል የአሰራር ስርዓት እንዲገባ እየተደረገ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን እንዳስታወቀው፤ ሶስተኛው የቅርስ ምርምር ጉባዔ ከሚያዝያ 13 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል።
የመጀመሪያው የቅርስ ምርምር ጉባዔ በ2016 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን፤ በ2017 ዓ.ም የተስተናገደው ሁለተኛው የቅርስ ምርምር ጉባዔ ከተለያዩ አገራት የተወጣጡ ምሁራን ጥናታዊ ጹሁፎች ያቀረቡበት እንደነበር ተገልጿል።
የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ በሰጡበት ወቅት፤ ሁለቱ ጉባዔዎች ኢትዮጵያ ምድረ ቀደምት ሀገርነቷን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
የዘንድሮው የቅርስ ምርምር ጉባዔውም "የኢትዮጵያ ቅርስ ምርምር በዲጂታል ዘመን" በሚል መሪ ሃሳብ ሚያዝያ 13 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሔድ ጠቁመዋል፡፡
የምርምር ጉባዔው በቅርስ ልማት ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን መርምሮ መፍትሄ ለመስጠት፣ አዳዲስ እውቀቶችን ለመለዋወጥ እና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህ የምርምር ጉባዔ ላይ 13 አዳዲስ የምርምር ጹሁፎች እንደሚቀርቡ ተናግረው፤ ጉባዔው የሚካሄደው በኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን አዳራሽ መሆኑን አስታውቀዋል።
ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት ቅርሶች ለአገር ኢኮኖሚ እድገት ጉልህ ድርሻ እያበረከቱ ይገኛሉ።
የቅርስ አሰባሰብን፣ አመዘጋገብንና የሙዚየም አገልግሎትን ለማዘመን በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የቅርስ አሰባሰብ፣ አመዘጋገብ እና አያያዝ ስርዓቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026