🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦የቅርስ ልማት እና ጥበቃ ስራ ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል የአሰራር ስርዓት እንዲገባ እየተደረገ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን እንዳስታወቀው፤ ሶስተኛው የቅርስ ምርምር ጉባዔ ከሚያዝያ 13 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል።
የመጀመሪያው የቅርስ ምርምር ጉባዔ በ2016 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን፤ በ2017 ዓ.ም የተስተናገደው ሁለተኛው የቅርስ ምርምር ጉባዔ ከተለያዩ አገራት የተወጣጡ ምሁራን ጥናታዊ ጹሁፎች ያቀረቡበት እንደነበር ተገልጿል።
የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ በሰጡበት ወቅት፤ ሁለቱ ጉባዔዎች ኢትዮጵያ ምድረ ቀደምት ሀገርነቷን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
የዘንድሮው የቅርስ ምርምር ጉባዔውም "የኢትዮጵያ ቅርስ ምርምር በዲጂታል ዘመን" በሚል መሪ ሃሳብ ሚያዝያ 13 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሔድ ጠቁመዋል፡፡
የምርምር ጉባዔው በቅርስ ልማት ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን መርምሮ መፍትሄ ለመስጠት፣ አዳዲስ እውቀቶችን ለመለዋወጥ እና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህ የምርምር ጉባዔ ላይ 13 አዳዲስ የምርምር ጹሁፎች እንደሚቀርቡ ተናግረው፤ ጉባዔው የሚካሄደው በኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን አዳራሽ መሆኑን አስታውቀዋል።
ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት ቅርሶች ለአገር ኢኮኖሚ እድገት ጉልህ ድርሻ እያበረከቱ ይገኛሉ።
የቅርስ አሰባሰብን፣ አመዘጋገብንና የሙዚየም አገልግሎትን ለማዘመን በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የቅርስ አሰባሰብ፣ አመዘጋገብ እና አያያዝ ስርዓቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026