🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 7/2018 (ኢዜአ)፦የቅርስ ልማት እና ጥበቃ ስራ ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል የአሰራር ስርዓት እንዲገባ እየተደረገ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር ገለጹ፡፡
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን እንዳስታወቀው፤ ሶስተኛው የቅርስ ምርምር ጉባዔ ከሚያዝያ 13 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል።
የመጀመሪያው የቅርስ ምርምር ጉባዔ በ2016 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን፤ በ2017 ዓ.ም የተስተናገደው ሁለተኛው የቅርስ ምርምር ጉባዔ ከተለያዩ አገራት የተወጣጡ ምሁራን ጥናታዊ ጹሁፎች ያቀረቡበት እንደነበር ተገልጿል።
የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኤሊያስ ሽኩር ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ በሰጡበት ወቅት፤ ሁለቱ ጉባዔዎች ኢትዮጵያ ምድረ ቀደምት ሀገርነቷን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
የዘንድሮው የቅርስ ምርምር ጉባዔውም "የኢትዮጵያ ቅርስ ምርምር በዲጂታል ዘመን" በሚል መሪ ሃሳብ ሚያዝያ 13 እስከ 14 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚካሔድ ጠቁመዋል፡፡
የምርምር ጉባዔው በቅርስ ልማት ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን መርምሮ መፍትሄ ለመስጠት፣ አዳዲስ እውቀቶችን ለመለዋወጥ እና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህ የምርምር ጉባዔ ላይ 13 አዳዲስ የምርምር ጹሁፎች እንደሚቀርቡ ተናግረው፤ ጉባዔው የሚካሄደው በኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን አዳራሽ መሆኑን አስታውቀዋል።
ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት ቅርሶች ለአገር ኢኮኖሚ እድገት ጉልህ ድርሻ እያበረከቱ ይገኛሉ።
የቅርስ አሰባሰብን፣ አመዘጋገብንና የሙዚየም አገልግሎትን ለማዘመን በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የቅርስ አሰባሰብ፣ አመዘጋገብ እና አያያዝ ስርዓቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026