🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል የጀመረችው ጉዞ በተግባር ስር እየሰደደ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ አሎማ ክላስተር በበጋ መስኖ የለማውን የደረሰ የስንዴ ማሳ ተመልክተዋል።

የመደመር መንግሥት ለበጋ መስኖና ለስንዴ ምርታማነት የሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሕይወት እየቀየረና የሀገርን የምግብ ሉዓላዊነት እያረጋገጠ እንደሚገኝም በመልዕክታቸው ጠቁመዋል።
ዛሬ የተመለከትነው የስንዴ ልማትም የራዕያችንን ውጤት፣ የሀሳባችን መሬት መንካትና ፍሬ የማግኘታችን ተጨባጭ ማሳያ ነው ብለዋል።

አርሶ አደሩን በተደመረ አቅም በማትጋትና የተፈጥሮ ፀጋዎቻችንን በመጠቀም በሁሉም መስክ ሀገርን የማሻገር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026