የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በአካባቢው ያለውን ልማት በከፍተኛ ደረጃ የሚያነቃቃ ነው 

Apr 17, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 8 /2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በአካባቢው ያለውን ልማት በከፍተኛ ደረጃ የሚያነቃቃ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።

የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዚህ ቀደም መመረቁ ይታወቃል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በሐይቅ ከተማ በመገኘት የሎጎ ሐይቅ ሪዞርትን ዛሬ ሥራ አስጀምረዋል።


የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት በክልሉ ያሉ ጸጋዎችን ወደ ተጨባጭ ልማት በመቀየር ሕዝቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።

የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀሳቦች መካከል አንዱ መሆኑን ገልጸው፤ ፕሮጀክቱ በከፍተኛ ርብርብ ለውጤት የበቃ፤ በአርአያነቱ የሚጠቀስ ነው ብለዋል።

ፕሮጀክቱ የአካባቢው ነዋሪዎች፣ መንግሥትና ተቋራጮች በጋራ በመሆን ያሳኩት፤ ሕዝብን በልማት ተጠቃሚ ለማድረግ ላለን ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

ወሎ የበርካታ ኃይማኖታዊ እና ታሪካዊ የቱሪስት መዳረሻዎች መገኛ ናት ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ወደ ሥራ መግባት ተጨማሪ የቱሪስት መዳረሻ በመሆን አቅም እንደሚፈጥር አብራርተዋል።

ፕሮጀክቱ በአካባቢው ለሚሰሩ ሌሎች ልማቶችም ምሳሌ እንደሚሆን ጠቁመው፤ ልማቱን በከፍተኛ ደረጃ የሚያነቃቃ መሆኑን ገልጸዋል።

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በበኩላቸው፤ ለውጡን ተከትሎ ልማቱ በሁሉም አካባቢዎች እንዲዳረስ መንግሥት የቀየሰው ሥልት ውጤት እያመጣ መሆኑን ተናግረዋል።


የሁለቱ ክልል ሕዝቦች በኢኮኖሚ እና ማህበራዊ መስኮች ዘመናትን የተሻገረ መስተጋብርና ትስስር ያላቸው መሆኑንም አንስተዋል።

በአማራ ክልል እየተመዘገበ ያለው ልማት በዘላቂነት ሕዝቡን ተጠቃሚ እንዲያደርግ ሰላም ወሳኝ መሆኑን አመልክተው፤ ለዚህም በክልሉ ያለው አመራር፣ የኃይማኖት አባቶች፣ ሴቶችና ወጣቶች በጋራ መሥራት ለነገ የሚባል ጉዳይ አይደለም ብለዋል።

የአፋር ክልልም በሰላም ዙሪያ ከአማራ ክልል ጋር አብሮ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

ባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ በበኩላቸው፤ በሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ግንባታ ተሳትፈን የታሪክ ተካፋይ የመሆን ዕድል በማግኘታችን ጥልቅ ደስታ ተሰምቶኛል ብለዋል።


በተለያዩ አካባቢዎች የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት ላይ በሰፊው እየተሳተፍን ነው ያሉት አቶ በላይነህ፤ በቀጣይም በልማት ዙሪያ ከመንግሥት ጋር በቅርበት ለመሥራት ቁርጠኛ ነን ሲሉ ተናግረዋል።

በትብብር መሥራት ከተቻለ የማይሳካ ነገር እንደሌለ የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ማሳያ መሆኑንም አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026