🔇Unmute
ሐዋሳ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሐዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማት የተፈጥሮ ፀጋዋን ከማጉላቱ ባለፈ የማኅበራዊ ትሥሥር መሰረት መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለፁ።
የሐዋሳ ከተማ 2ኛና 3ኛ ዙር የኮሪደር ልማት ሥራ ማጠናቀቂያ እና የ4ኛ ዙር የኮሪደርና የሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር ተካሂዷል።

በዚሁ ወቅት ከንቲባው እንዳሉት፤ የሐዋሳን የቱሪዝምና ኮንፈረንስ ማዕከልነት ለማጠናከር ሥራዎች በተሻለ ፍጥነትና ጥራት መከናወናቸው ይቀጥላል።
የከተማዋ የኮሪደር ልማት ያላትን የተፈጥሮ ፀጋ አጉልቶ ከማውጣቱ በተጨማሪ፤ የቱሪዝም መስኅብና የማኅበራዊ ትሥሥር መሠረት እየሆነ ነው ብለዋል።
የግንባታ ሥራው ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቃው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ውበትና የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ያረጋገጠ መሆኑንም አንስተዋል።
4ኛው ዙር የኮሪደር ልማት 3 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር እንደሚሸፍን ጠቁመው፤ የሐይቅ ዳርቻ ልማቱም የሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻን ይዞ እንደሚለማ አመላክተዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026