🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ኢትዮጵያ ያከናወነችው ሪፎርም ያመጣውን መሻሻል በማድነቅ ለሀገሪቱ የሪፎርም አጀንዳ ያለውን ጠንካራ ድጋፍ ዳግም አረጋግጧል።
በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ ጋር ተወያይቷል።
ውይይቱ የተካሄደው፤ ከ2026 የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም የፀደይ ስብሰባ ጎን ለጎን መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ የላከው መረጃ አመላክቷል።
በምክክሩ ወቅትም፤ በኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አማካኝነት እየተመዘገቡ ያሉ ቀጣይነት ያላቸው ውጤቶችን ልዑኩ አብራርቷል።
ለአብነትም በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጠንካራ የኢኮኖሚ ዕድገትና የዋጋ ግሽበት መቀነስን ጨምሮ ሌሎች አዎንታዊ አዝማሚያዎች መታየታቸውን ጠቁሟል።
ሪፎርሙ በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተውን ወቅታዊ ሁኔታ ጨምሮ የሚከሰቱ ውጫዊ ተፅዕኖዎችን ተቋቁሞ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉም ተብራርቷል።
ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊ ችግሮች ከአቅርቦት ሰንሰለት መስተጓጎል፣ ከነዳጅ ብሎም ማዳበሪያ ዋጋ መናር ጋር ተያይዞ ጫናዎች መኖራቸውም እንዲሁ።
እነዚህን ወቅታዊ ችግሮች ለመሻገርም የተጠናከረ ዓለም አቀፍ ድጋፍ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝቧል።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ያከናወነችው ሪፎርም ያመጣውን መሻሻል በማድነቅ፤ተቋማቸው ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር ሪፎርሙን ለማስቀጠል እና የፋይናንስ ፍላጎቶችን ለማሟላት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል።
#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026