የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

መንግሥት የጠራ ፖሊሲ ሲኖረው ፍሬያማ ሥራ ሊሠራ እንደሚችል የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ያሳያሉ

Apr 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የጠራ ፖሊሲ ሲኖረውና ማስፈጸሚያ ስትራቴጂው ያን ለመመገብ የሚያስችል ሲሆን ምን ዓይነት ፍሬያማ ሥራ ሊሠራ እንደሚችል የተጀመሩ አጠቃላይ እንቅስቃሴዎች ያመላክታሉ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ የሐሮ ደንዲ ሎጅን የመረቁ ሲሆን፤ ከምረቃው በኋላም ማብራሪያ ሰጥተዋል።


በማብራሪያቸውም፤መንግሥት የጠራ ፖሊሲ ሲኖረው፣ ማስፈጸሚያ ስትራቴጂው ያን ለመመገብ የሚያስችል ሲሆን እና የማስፈጸም ዐቅም በተቋም ደረጃ እየገነባ ሲሄድ ምን ዓይነት ፍሬያማ ሥራ ሊሠራ እንደሚችል ኢትዮጵያ ውስጥ የተጀመሩ አጠቃላይ እንቅስቃሴዎች ያመላክታሉ ብለዋል።

እንደ ሀገር አምሥት ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶ ብለን የለየናቸው ሴክተሮችን ብንመለከት፤ ከፖሊሲ፣ከስትራቴጂ እና ከአፈጻጸም አንጻር ከፍተኛ ውጤት እያስገኙ ይገኛሉ ሲሉም አብራርተዋል።

ለአብነትም ከኢንዱስትሪ አንጻር፤ ቀደም ሲል መንግሥት ኢንዱስትሪያል ፓርክ ይገነባ እንደነበር አውስተው አሁን ግን የኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት የሚችሉ የግል ሴክተሮች መፍጠር መቻሉን አንስተዋል።

በርካታ ፋብሪካዎች፣ ኢንዱስትሪል ፓርኮች፣ ዘመናዊ ኢንዱስትሪዎች መሥራት ስንጀምርም፤ ከውጭ የምናስገባቸውን ምርቶች በሀገር ውስጥ በማምረት ወደ ውጭ የምንልከውን ቁጥርም ለማሳደግ በእጅጉ አግዘዋል ነው ያሉት።


ከግብርና አንጻር ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረው ግብርና በርካታ ችግሮች እንደነበሩበት አውስተው፤ በሚሊዮን የሚቆጠር አርሶ አደርን በክላስተር በማደራጀት ትራክተር፣ ኮምባይነር፣ ፓምፕና የተለያዩ ማሽነሪዎችን ማቅረብ ስንችል አነስተኛ አርሶ አደሮች በሚያርሷቸው ማሳዎች ጭምር የሚገኘው ምርት አድጓል ብለዋል።

የግል ሴክተሩም በዚያው ልክ ኢንቨስት ማድረግ እየጀመረ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል። ለምሳሌ ቡናን ብንመለከት፤100 ሺህ ሔክታር ገደማ መሬት የግል ሴክተሩ ወስዷል፤ ይህን በመስኖ ከሠሩ የምናመርተውን ግማሽ ያህል ሊያመርቱ ይችላሉ ነው ያሉት።

በአጠቃላይ በግብርናው ዘርፍ በርካታ ውጤቶች መገኘታቸውን በመግለጽ፤ይህም በፍጆታችን ብቻ ሳይሆን በኤክስፖርታችን የሚታይ ሆኗል ሲሉ አስገንዝበዋል።

በማዕድን ዘርፍም፤ቀደም ሲል በዘርፉ ሊጠቀስ የሚችል ሥራ አለ ለማለት እንደሚከብድ በመጠቆም፤ ኤክስፖርቱም ውስን እንደነበር አንስተዋል።

አሁን ግን በወርቅ፣ በማዳበሪያ፣ በጋዝ፣ በሴራሚክ፣ በሲሚንቶ ዘርፎች መንግሥት ዐይን ሲገልጥና ሲያመቻች የግል ሴክተሩ ተሳትፎ ምን ሊያመጣ እንደሚችል ውጤቱ ያሳያል ብለዋል።

የማዕድን ሴክተሩ ፖሊሲ ላይ ባስቀመጥነው ልክ ውጤቱ በኤክስፖርት ውጤታችን ጭምር እየታየ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

ከቴክኖሎጂ አንጻርም፤ እየተሠራ ያለው ሥራ ሞባይል ማስፋት፣ ዳታ ማስፋት ብቻ እንዳልሆነ አስገንዝበዋል።

ስለሆነም በቴሌኮም ብቻ የነበረውን ሌላ ተቋም (ሳፋሪኮም) ስናመጣ ውድድር ሲጀመር፣ ኤ አይ ሲጨመር፣ መሶብ ሲታከል፣ 5 ሚሊየን ኮደሮች ሲጨመር ዘርፉ ኢኮኖሚያችንን የሚያነቃቃና የሚያስተሳስር እየሆነ መጥቷል ነው ያሉት በማብራሪያቸው።

ከቱሪዝም አንጻርም ኢትዮጵያ ያላትን ታሪክና ባህል ማሳየት የሚያስችል መሠረተ-ልማት እንዳልነበረ አንስተዋል። ይህን እንቀይር የሚል እሳቤ ተይዞ ወደ ሥራ መገባቱንም በመግለጽ።


በዚህም መሠረት፤በገበታ ለሸገር፣በገበታ ለሀገር፣ በገበታ ለትውልድ ባለሃብት አስተባብረን የሠራናቸው ሥራዎች፤የቱሪዝም ሴክተሩን አስተምረን ዐይን ገልጠን ወደ ግል ሴክተር እንዲገባ ማድረግ አለብን የሚል ነበር ብለዋል።

በዚህም በርካታ ቦታዎች በገበታ ኢንሼቲቭ መሠራታቸውን እና በዚያው ልክ የግል ሴክተሩ መግባቱን ጠቅሰዋል።

በቅርቡ ለኮፕ 32 ስንወያይም አሁን 20 ሺህ ገደማ ያለው ለእንግዶች የሚሆን የአልጋ ዐቅማችንን ወደ 80 ሺህ ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች ኢትዮጵያ ውስጥ እየተሠሩ መሆኑን አይተናል፤ይህም ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።

በዚህ ላይ ኤርፖርቱ፣ኢነርጂው፣ መንገዱ እየተጨማመረ እየመገበው ሲሄድ፤ አጠቃላይ ፖሊሲውን በከፍተኛ ደረጃ አጉልቶ ያሳያል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026