🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦አሜሪካ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትራስፎርሜሽን የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል አስታወቀች።
በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን፣በዋሺንግተን ዲሲ ከተካሄደው የዓለም ባንክ እና የአይኤምኤፍ (IMF) የፀደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን፣ከከፍተኛ የአሜሪካ የግምጃ ቤት መሥሪያ ቤት ባለሥልጣናት ጋር በኢኮኖሚያዊ ትብብር ዙሪያ ተወያይቷል።
ውይይቱ በዋነኝነት ያተኮረው የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነቶችን በማሳደግ ላይ ሲሆን፣ በተለይም እንደ አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ያሉ ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።
የአሜሪካ ባለሥልጣናት ኢትዮጵያ እያከናወነች ያለችውን የኢኮኖሚ ሪፎርም አበረታች ሂደት አድንቀዋል።
ባለሥልጣናቱ አሜሪካ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን የምታደርገውን ድጋፍ በቴክኒክ ድጋፍ፣ በግሉ ዘርፍ ተሳትፎ እና ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር እንደምታጠናክርም በድጋሚ አረጋግጠዋል።
ሁለቱም ወገኖች ቅድሚያ በሚሰጧቸው የጋራ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ወደፊት ለማራመድ፣ ዕድገትን ለማፋጠን እና የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ትስስር ለማስፋት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026