የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አሜሪካ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን የምታደርገውን ድጋፍ ለማጠናከር ቁርጠኝነቷን ገለጸች

Apr 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 12/2018 (ኢዜአ)፦አሜሪካ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትራስፎርሜሽን የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል አስታወቀች።

በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን፣በዋሺንግተን ዲሲ ከተካሄደው የዓለም ባንክ እና የአይኤምኤፍ (IMF) የፀደይ ወቅት ስብሰባ ጎን ለጎን፣ከከፍተኛ የአሜሪካ የግምጃ ቤት መሥሪያ ቤት ባለሥልጣናት ጋር በኢኮኖሚያዊ ትብብር ዙሪያ ተወያይቷል።

ውይይቱ በዋነኝነት ያተኮረው የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነቶችን በማሳደግ ላይ ሲሆን፣ በተለይም እንደ አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ያሉ ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።

የአሜሪካ ባለሥልጣናት ኢትዮጵያ እያከናወነች ያለችውን የኢኮኖሚ ሪፎርም አበረታች ሂደት አድንቀዋል።

ባለሥልጣናቱ አሜሪካ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን የምታደርገውን ድጋፍ በቴክኒክ ድጋፍ፣ በግሉ ዘርፍ ተሳትፎ እና ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር እንደምታጠናክርም በድጋሚ አረጋግጠዋል።

ሁለቱም ወገኖች ቅድሚያ በሚሰጧቸው የጋራ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ወደፊት ለማራመድ፣ ዕድገትን ለማፋጠን እና የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ትስስር ለማስፋት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026