🔇Unmute
አርባ ምንጭ፤ ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ያሉ የኢንዱስትሪ ዐቅሞችን ለይቶ ጥቅም ላይ ለማዋል ጥናትን መሠረት ያደረገ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ርዕሠ መሥተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
ሀገራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት እምቅ ዐቅም ፍኖተ ካርታ ላይ የሚመክር መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው።
ርዕሠ መሥተዳድር ጥላሁን በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ በክልሉ የሚገኙ የኢንዱስትሪ ዐቅሞችን ለይቶ በማልማት ጥቅም ላይ ለማዋል በጥናት ላይ የተመሠረተ ሥራ እየተሠራ ነው።
ለክልሉ ብሎም ለሀገር ሁለንተናዊ ብልጽግና መረጋገጥ የአምራች ኢንዱስትሪው ሚና ጉልህ መሆኑን ገልጸው፤ በክልሉ በርካታ የኢንዱስትሪ አማራጮች እንዳሉ አመላክተዋል።
የለውጡ መንግሥት በተከተለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም በርካታ ለውጦች መምጣታቸውንም ጠቁመዋል።
ማኑፋክቸርንግ ኢንዱስትሪው በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በተኪ እና ወጪ ምርቶች ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ አሳይቷልም ብልዋል።
ክልሉን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የሰነቅነው ራዕይ እንዲሳካ በየደረጃው ያለው አመራር በኢንዱስትሪው ዘርፍ የበኩሉን አስተዋጾ እንዲያበረክትም አሳስበዋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴዔታ ታረቀኝ ቡሉልታ በበኩላቸው፤ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ለኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር የማይተካ ሚና እንዳለው አስገንዝበዋል።
መንግሥት ለኢንዱስትሪ ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠቱ እና ተወዳዳሪ የሚያደርግ የኢንዱስትሪ ፖሊሲና ግልጽ መርሆዎች በማስቀመጡ ዘርፉ ስኬታማ እየሆነ መምጣቱን አስረድተዋል።
ለዚህም የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢንዱስትሪዎች በሙሉ ዐቅማቸው እንዲያመርቱ ከፍተኛ መነቃቃት መፍጠሩን ነው ያስረዱት።
በዚሁም የአምራች ኢንዱስትሪው የማምረት ዐቅም ከዚህ ቀደም ከነበረበት ወደ 66 ነጥብ 3 በመቶ ማደጉን አብራርተዋል።
ከተኪ ምርት አኳያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 4 ነጥብ 65 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ግምት ያለው ምርት መተካት እንደተቻለ ጠቁመው፤ በዘርፉ ከ202 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል።

ክልሉ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ሰፊ ዐቅም ስላለው ሁሉም ኢንዱስትሪዎች በሙሉ ዐቅማቸው እንዲያመርቱ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሰናይት ሰለሞን ናቸው።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026