የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥና የራስን አቅም የመገንባት ታሪካዊ ጉዞ ነው 

Apr 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 15/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገርን የኢኮኖሚ ነፃነት በማረጋገጥ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ታሪካዊ ጉዞ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።

ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ይህን የተናገሩት "ድሬ ታምርት ኢትዮጵያ ትበልፅግ" በሚል መሪ ሃሳብ በተዘጋጀው የአምራች ኢንዱስትሪዎች ኤክስፖ የፓናል ውይይት ላይ ነው።


አቶ መላኩ በወቅቱም፤ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ በተደረገው ድጋፍና ክትትል እመርታዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ተናግረዋል።

በንቅናቄው የተዘጉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ እንዲመለሱ በማድረግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በጥራትና በስፋት እየተተኩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት፣ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ እና የስራ ዕድል በመፍጠር ረገድም መሠረታዊ ውጤቶች መገኘታቸውን በመጥቀስ።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገርን የኢኮኖሚ ነፃነት በማረጋገጥ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ታሪካዊ ጉዞ መሆኑን በአፅንኦት ገልጸዋል።

በሌሎች ሀገራት አልባሳት፣ መድኃኒት፣ መገልገያዎችና ሌሎች ምርቶች ላይ ጥገኛ የሆነ አገር ሉዓላዊነቱን ማረጋገጥ እንደማይችል በማመላከት።

በንቅናቄው በተሰሩ ስራዎች በዘንድሮ በጀት ዓመት ብቻ 13 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ የውጭ ሀገራት ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በዘርፉ ለመሰማራት መዘጋጀታቸውን አስታውሰዋል።

ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግና በኢኮኖሚው ውስጥ የመሪነት ድርሻውን እንዲያረጋግጥ የህግና የፖሊሲ ማሻሻያዎች እየተደረጉ ይገኛሉም ብለዋል።


የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች በተደረጉ ድጋፎች ተዘግተው የነበሩ 15 ከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ማምረት በማሸጋገር ከ9 ሺህ 200 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ቋሚ የስራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸዋል።

አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ተኪ እና ወጪ ምርቶችን በስፋትና በጥራት እያመረቱ መሆኑን ጠቅሰው ከንቅናቄው በኋላ የኢንዱስትሪዎቹ የማምረት አቅም ከ42 በመቶ ወደ ወደ 64 በመቶ ከፍ ማለቱን አንስተዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ፤ ባለፉት አራት ዓመታት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተሰሩ ስራዎች ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ማስቻላቸውን ገልፀዋል።


በተደረጉ ሁሉን አቀፍ ድጋፎችና ክትትሎች የተዘጉ እና በግንባታ ላይ ያሉ ፋብሪካዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን በማስታወስ።

ባለፉት ዓመታት 253 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ከ2 ሺህ 620 በላይ ባለሃብቶች ፍቃድ ወስደው ወደ ዘርፉ መግባታቸውን ጠቅሰው ወደ ማምረት የተሸጋገሩትም ከ10ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥረዋል ብለዋል።

በፓናል ውይይቱ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ባለቤቶች፣ የኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026