የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ፈጣን እና ጊዜ ቆጣቢ ነው- ተገልጋዮች

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፦መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ወደ እኛ ከመቅረቡም ባለፈ ፈጣን እና ጊዜ ቆጣቢ ሆኖ አግኝተነዋል ሲሉ ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአገልግሎት ቅልጥፍናንና ተደራሽነትን ለማሻሻል ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ የታመነበትን መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት በይፋ መርቀው ሥራ ማስጀመራቸው ይታወቃል።

በምረቃው ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት፤ ቴክኖሎጂን ለአገልግሎት ዘርፉ እንደ ዋነኛ መሣሪያ በመጠቀም ዜጎች ጊዜ ቆጣቢ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል በቁርጠኝነት እየተሠራ ይገኛል።


የመሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት አጭር ጊዜ ቢሆንም፤ በአገልግሎቱ የታየው ከፍተኛ የደንበኞች እርካታ የሥራ ሞዴሉን ውጤታማነት በተግባር ማረጋገጡንም ጠቁመዋል።

መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጀርመን አደባባይ አካባቢ ለህዝቡ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

በዚሁ ወቅት ኢዜአ ያነጋገራቸው ተገልጋዮች አገልግሎቱ ፈጣን እና ጊዜ ቆጣቢ መሆኑን ተናግረዋል።

አቶ ኢብራሂም መሐመድ የመኪና ቦሎ ለማደስ ወደ ቦታው መሄዳቸውን ጠቁመው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳያቸውን ጨርሰው መመለሳቸውን ተናግረዋል።


አቶ ብስራት ኮሬ እና አቶ ዘላለም አስረስም ለመንጃ ፈቃድና ለቦሎ ዕድሳት ወደ ተንቀሳቃሽ አውቶቡሱ በማቅናት፣ በአይነቱ ልዩና ቀልጣፋ መስተንግዶ ማግኘት መቻላቸውን ተናግረዋል።


ያለምንም ስጋት ጊዜያቸውንም ቆጥበው በአገልግሎቱ ተጠቃሚ በመሆናቸው መደሰታቸውን ይናገራሉ።


በተንቀሳቃሽ አገልግሎቱ ውስጥ የሚሰሩት የገቢዎች ባለሙያ ጫልቱ ታደሰ፣ ይህ አሰራር የተለመደውን በአንድ ቦታ ተወስኖ የመስራት አካሄድ በመቀየር ለተገልጋዩ ብቻ ሳይሆን ለአገልጋዩም ከፍተኛ የስራ ተነሳሽነትን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።


የንግድ ምዝገባ እና ፍቃድ ባለሙያ ብርሃኑ ፈንታው በበኩላቸው፣ ወደ ተገልጋዮች ቀርበው በቴክኖሎጂ የታገዘ ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የመጀመሪያዎቹ ባለሙያዎች በመሆናቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።


የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ካባ መብራቱ፤ የመሶብ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ቀደም ሲል በሕዝብ ዘንድ ይነሳ የነበረውን ቅሬታ ለመፍታት መንግሥት የወሰደውን ቁርጠኛ አቋም የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።


አዲሱ እሳቤ አገልግሎትን ከቢሮ በማውጣት ወደ ሕዝብ ይዞ የመጣ ድንቅ አሠራር መሆኑን አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026