🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ) ፦ በሀረሪ ክልል በገጠር ኮሪደር ልማት ሁለተኛው ዙር ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር ግንባታ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በተገኙበት ተጀምሯል።
ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ሞዴል የአርሶ አደሮች የመኖሪያ መንደር ግንባታ ባስጀመሩበት ወቅት እንዳሉት የክልሉ መንግስት ከመቼውም ጊዜ በላቀ ሁኔታ የዜጎችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
በኮሪደር ልማቱ ሀረር ከተማን ተምሳሌት እንድትሆን ያስቻሉ ውጤታማ ስራዎች እንደተከናወኑ ሁሉ ስኬቱን በገጠር ኮሪደር ልማትም በክልሉ የተለያዩ ወረዳዎች ለመድገም እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ በተለያዩ ወረዳዎች የሚከናወኑ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራዎች አስፈላጊው የመሰረተ ልማት እንዲሟላ ከማድረግ ባለፈ አርሶ አደሩ ዘመናዊና የተመቸ ኑሮ እንዲመራ ያስችላል ሲሉም ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደምም በገጠር ኮሪደር ልማት የቤት ቁሳቁስ የተሟላላቸው ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶች ተገንብተው ለአርሶ አደሮች እንዲተላለፉ መደረጉን አንስተዋል።
በሁለተኛው ዙር ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር ፕሮጀክትም 250 ቤቶች እንደሚገነቡ ጠቁመዋል።

ሞዴል የአርሶ አደሮች መንደር ግንባታ አካባቢያዊ ሀብቶችን በመጠቀም እውን እንደሚደረግ ጠቁመው በየአካባቢው የሚገኙ አርሶ አደሮችም ለፕሮጀክቱ መሳካት እንደከዚህ ቀደሙ በቅንጅት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ከዚህ በተጨማሪም በክልሉ በከተማና በገጠር እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026