🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አሰራሩን በቴክኖሎጂ በማዘመን በታላቅ የሽግግር ሂደት ላይ እንደሚገኝ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እያከናወነ የሚገኘውን የሪፎርም ሥራዎች ጎብኝተዋል።

ከንቲባዋ በጉብኝቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ከተማ አስተዳደሩ ለተቋም ግንባታ የሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው ብለዋል።
ተቋማት ቀጣይነት ያለው ሥራ እንዲሰሩና የአገልግሎት አሰጣጣቸውም ዘላቂ እንዲሆን የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ትልቅ ማሣያ ነው ብለዋል።
ተቋሙ ከቅጣት ይልቅ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መስጠት ላይ እየሰራ መሆኑን አብራርተው፤ የደንብ ጥሰት ተፈጽሞ ሲገኝ ብቻ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ባለስልጣኑ በቴክኖሎጂ ራሱን በማዘመንና በመረጃ ላይ በመመስረት ሕግና ሥርዓትን ወደ ማስከበር መሸጋገሩን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ባለስልጣኑ ወረቀት አልባ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የከተማዋ የስማርት ሲቲ ግንባታ አንዱ አካል መሆኑን ገልጸዋል።
አሰራሩን በሞባይል መተግበሪያም ጭምር በመስጠት ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ መጀመሩንም ተናግረዋል።

ማህብረሰቡ የደንብ ጥሰት ሲፈጸም ካለበት ቦታ ሆኖ ጥቆማ የሚሰጥበት ዘመናዊ አሰራር መዘርጋቱንም ጠቅሰዋል።
የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አሰራሩን በማዘመን በታላቅ የሽግግር ሂደት ላይ እንደሚገኝም አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026