የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አሰራሩን በማዘመን በታላቅ የሽግግር ሂደት ላይ ይገኛል -ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Apr 30, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አሰራሩን በቴክኖሎጂ በማዘመን በታላቅ የሽግግር ሂደት ላይ እንደሚገኝ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እያከናወነ የሚገኘውን የሪፎርም ሥራዎች ጎብኝተዋል።


ከንቲባዋ በጉብኝቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ከተማ አስተዳደሩ ለተቋም ግንባታ የሰጠው ትኩረት ተጨባጭ ውጤት እያመጣ ነው ብለዋል።

ተቋማት ቀጣይነት ያለው ሥራ እንዲሰሩና የአገልግሎት አሰጣጣቸውም ዘላቂ እንዲሆን የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ትልቅ ማሣያ ነው ብለዋል።

ተቋሙ ከቅጣት ይልቅ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መስጠት ላይ እየሰራ መሆኑን አብራርተው፤ የደንብ ጥሰት ተፈጽሞ ሲገኝ ብቻ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ባለስልጣኑ በቴክኖሎጂ ራሱን በማዘመንና በመረጃ ላይ በመመስረት ሕግና ሥርዓትን ወደ ማስከበር መሸጋገሩን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት ባለስልጣኑ ወረቀት አልባ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የከተማዋ የስማርት ሲቲ ግንባታ አንዱ አካል መሆኑን ገልጸዋል።

አሰራሩን በሞባይል መተግበሪያም ጭምር በመስጠት ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ መጀመሩንም ተናግረዋል።


ማህብረሰቡ የደንብ ጥሰት ሲፈጸም ካለበት ቦታ ሆኖ ጥቆማ የሚሰጥበት ዘመናዊ አሰራር መዘርጋቱንም ጠቅሰዋል።

የደንብ ማስከበር ባለስልጣን አሰራሩን በማዘመን በታላቅ የሽግግር ሂደት ላይ እንደሚገኝም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026