🔇Unmute
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከተለያየ የገቢ አርዕስት ከ3 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቸንኮት ዴቪድ ገለጹ።
በተያዘው የበጀት ዓመት ከተለያየ የገቢ አርዕስት ከ7 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ግብ ተጥሎ እየተሠራ መሆኑን ኃላፊው ለኢዜአ ተናግረዋል።
በዚህም መሠረት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ የነበሩ ፈተናዎችን በመቋቋም ከቀጥታ ታክስ፣ ቀጥታ ካልሆኑና ከሌሎች የገቢ አርዕስት ከ 3 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አረጋግጠዋል።
ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ1 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ብልጫ አለው ብለዋል።
የተጀመሩ የገቢ አሰባሰብ ተግባራትን በማጠናከር ዓመታዊ ዕቅዱን ለማሳካት ርብርብ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።
ግብር መክፈል ሕዝቡ የሚፈለገውን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሠረተ-ልማቶችን ለማሟላት ያለው ፋይዳ የጎላ በመሆኑ፤ ዜጎች የሚጠበቅባቸውን ግብር በመክፈል ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026