🔇Unmute
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከተለያየ የገቢ አርዕስት ከ3 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቸንኮት ዴቪድ ገለጹ።
በተያዘው የበጀት ዓመት ከተለያየ የገቢ አርዕስት ከ7 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ግብ ተጥሎ እየተሠራ መሆኑን ኃላፊው ለኢዜአ ተናግረዋል።
በዚህም መሠረት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ የነበሩ ፈተናዎችን በመቋቋም ከቀጥታ ታክስ፣ ቀጥታ ካልሆኑና ከሌሎች የገቢ አርዕስት ከ 3 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አረጋግጠዋል።
ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ1 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር በላይ ብልጫ አለው ብለዋል።
የተጀመሩ የገቢ አሰባሰብ ተግባራትን በማጠናከር ዓመታዊ ዕቅዱን ለማሳካት ርብርብ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።
ግብር መክፈል ሕዝቡ የሚፈለገውን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሠረተ-ልማቶችን ለማሟላት ያለው ፋይዳ የጎላ በመሆኑ፤ ዜጎች የሚጠበቅባቸውን ግብር በመክፈል ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026