የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአሪ ዞን በዘንድሮ የበልግ እርሻ ከ51 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ለምቷል

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ ሚያዚያ 28/2018(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን በዘንድሮ የበልግ እርሻ ከ51 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በተለያዩ ሰብሎች መልማቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።


የመምሪያው ኃላፊ ጉራልቅ ይዥማልቅ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በበልግ አዝመራው እየለማ ካለው መሬት ውስጥ ከ3 ነጥብ 8 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ብለዋል።


አርሶ አደሩ ከመደበኛው የሰብል ምርት በተጨማሪ የተሻሻሉ የስንዴ፣ የማሽላ እና የበቆሎ ምርጥ ዘሮችን በኩታገጠም በስፋት በማልማት ለሌሎች አካባቢዎች እያቀረቡ መሆኑንም ገልፀዋል።


ዞኑ የተለያዩ የአየር ፀባዮች ያለው በመሆኑም በተለይ በደጋው አካባቢ ስንዴ፣ ገብስ፣ ባቄላ እና አተር እየተመረተ መሆኑንም አስታውቀዋል።


ወይናደጋ እና ቆላማ በሆኑት አካባቢዎች ደግሞ ጤፍ፣ ማሽላ፣ በቆሎ፣ ሩዝ፣ ለውዝ፣ ሰሊጥ፣ ማሾ እና መሰል ሰብሎች በስፋት እየለማ መሆኑንም አመልክተዋል።


በአሁኑ ወቅትም አርሶ አደሩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ ምርታማነቱን እንዲያሻሽል በማሰልጠኛ ማዕከላት ተግባር ተኮር ትምህርት እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።


በዞኑ የባካ ዳውላ አሪ ወረዳ አርሶ አደር ማርቆስ አዲሱ፥ በዘንድሮው የበልግ አዝመራ በቆሎና በአጭር ጊዜ የሚደርሱ የጓሮ አትክልቶችንም በማልማት የገቢ አቅማቸውን ማሳደጋቸውን ነው የሚገልጹት።


ሌላው አርሶ አደር ግርማ ከማይ በበኩላቸው፤ በዘንድሮው የበልግ አዝመራ ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመጣመር በ10 ሄክታር መሬት ላይ በኩታ ገጠም ስንዴ እያለሙ እንደሚገኙ ተናግረዋል።


ከጥቂት ጊዜ ወዲህ የስንዴ ምርት በኢንዱስትሪውም ሆነ በማሕበሩ በስፋት የሚፈለግ በመሆኑ በዘርፉ መስራታቸው ውጤታማ እያደረጋቸው መምጣቱን ጠቁመዋል።


ከግብርና ባለሙያዎች የሚሰጧቸውን ምክረ ሀሳቦች በመተግበራቸውም ምርትና ምርታማነታቸውን እንዳሳደገላቸው ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026