የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ሀገራዊ ዕድገትን የሚያሳልጡ የማኑፋክቸሪንግ ምርቶችን በማየታችን ኮርተናል 

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ሀገራዊ ዕድገትን የሚያሳልጡ የማኑፋክቸሪንግ ምርቶችን በመመልከታቸው ኩራት እንደተሰማቸው የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች እና አባላት ገለጹ፡፡

የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች እና አባላት "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደውን አራተኛውን የኢትዮጵያ ታምርት ዓለም አቀፍ ኤክስፖ ጎብኝተዋል፡፡


የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በዚህ ወቅት፤ በኤክስፖው በኢንዱስትሪው ዘርፍ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የሚያሳልጡ ተግባራት መከናወናቸውን መመልከታቸውን ገልጸዋል።


ኢትዮጵያ ወደ ዲጂታል ስርዓት የምታደርገውን ግስጋሴ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ቴክኖሎጂዎችን ተመልክተናል ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የዜጎችን ምርታማነት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸው፤ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤው ምርታማነት በዘላቂነት እንዲረጋገጥ በሰላም ላይ አተኩሮ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ፤ ኢትዮጵያ በርካታ ምርቶችን ከውጭ የምታስገባ ሀገር ሆና መቆየቷን አንስተዋል፡፡


ይሁን እንጂ የተለያዩ ምርቶችን በሀገር ሀብትና የሰው ሃይል ማምረት የሚያስችል አቅም መፈጠሩን መመልከታቸውን ገልጸው፤ በጉብኝታችን ኢትዮጵያ በዕድገት ጎዳና ላይ እንዳለች ተገንዝበናል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ጽህፈት ቤት ጠቅላይ ጸሀፊ አባ አብርሃም ገብረማርያም፤ ኢትዮጵያውያን የሀገር ውስጥ ምርትን የመጠቀም ባህላችንን ልናጎለብት ይገባል ብለዋል፡፡


ትልውዱ ለአምራችነት ልዩ ትኩረት በመስጠት የሀገር ውስጥ ምርትን የመጠቀም ባህሉን እንዲያዳብር የአባትነት ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ምክትል ፕሬዝዳንት ፓስተር ታሪኩ ብርሀኑ፤ ኢትዮጵያ ከውጭ የምታስገባውን ምርት በሀገር ውስጥ ለመተካት የምታደርገው ጥረት አስደናቂ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


ተኪ ምርቶችን በስፋት ማምረት ኢትዮጵያን ከድህነት ለማውጣት የሚደረገው ጥረት ፍሬያማ እንዲሆን ያግዛልም ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026