የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በርካታ ሰዎችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት ማሸጋገር ያስቻለው የከተማ ግብርና

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በከተማ ግብርና ዘርፍ በተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት በርካቶችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት ማሸጋገር መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ኮሚሽን አስታወቀ።

ባለፉት ዓመታት በተሰሩ ስራዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የከተማ ግብርና ቤተሰብ መፍጠር መቻሉንም ጠቁሟል፡፡

በከተማ ግብርና እየተሳተፉ የሚገኙ ዜጎች በበኩላቸው፤ በዘርፉ በመሰማራታቸው ከዕለታዊ ፍጆታ ባለፈ ሌሎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን ይናገራሉ።

በከተማ ግብርና የተሰማሩ ዜጎች በበኩላቸው፤ ከራሳቸው ፍጆታ ባለፈ ለሌሎች ማኅበረሰብ ክፍሎች ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

የከተማ ግብርና ስትራቴጂዎች ሀገራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጉዞ፣ ዜጎች በራሳቸው አቅም ምግብን ማምረት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየና የሥራ ባህልን የቀየረ ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው፡፡

ይህ የተቀናጀ ጥረት ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በምግብ ራስን ለመቻልና ከድህነት ለመውጣት ለጀመረችው ጉዞ እንደ ትልቅ ስኬት የሚወሰድ ነው።


የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ባዩ ሽጉጤ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በከተማ ግብርና በተከናወኑ ተግባራት ዜጎችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመለወጥ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በመዲናዋ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የሚገኙና ቀደም ሲል የሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚ የነበሩ የማኅበረሰብ ክፍሎች፣ ወደ አምራችነት እንዲሸጋገሩ መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡

ይህም በከተማ ግብርና አይቻልም የሚለውን የተሳሳተ አመለካከት በመቀየር፣ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የከተማ ግብርና ተጠቃሚ ቤተሰቦችን መፍጠር ማቻሉንም ጠቁመዋል፡፡

በተመሣሣይ ከሁለት ሺህ ሰባት መቶ በላይ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በተቀናጀ ሁኔታ በከተማ ግብርና ላይ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል።

በመዲናዋ በከተማ ግብርና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ያላቸውን ዜጎች ተጠቃሚ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በከተማ ግብርና በአነስተኛ ቦታ ላይ በማምረት ከራስ ፍጆታ አልፎ ለገበያ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርት ማቅረብ መጀመሩንም ጠቁመዋል።

በከተማ ግብርና እየተሳተፉ የሚገኙ ዜጎች በበኩላቸው፤ በዘርፉ በመሰማራታቸው ከዕለታዊ ፍጆታ ባለፈ ሌሎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን ይናገራሉ።

ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ሸምሱ ነጋሽ፤ ቀደም ሲል በሴፍቲኔት ፕሮግራም ተረጂ እንደነበሩ አስታውሰው፣ መንግሥት ባመቻቸላቸው ዕድል ወደ ከተማ ግብርና በመግባት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ወይዘሮ መይሙና ጀማል በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል ምንም ዓይነት የገቢ ምንጭ እንዳልነበራቸው አስታውሰው፤ አሁን በከተማ ግብርና ተሰማርተው ውጤታማ እየሆኑ መመጣታቸውን ተናግረዋል።


ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ወጣት ሽመልስ ድሪባ፤ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ከጓደኞቹ ጋር በመደራጀት ውጤታማ ሥራ እየሠራ መሆኑን ገልጿል።

ከመንግሥት ባገኙት ብድር አምስት ላሞች ገዝተው ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቅሶ በአሁኑ ወቅት የላሞቻቸው ቁጥር ከ20 በላይ መድረሱንና ለሌሎች ወጣቶችም የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ተናግሯል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026