የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በርካታ ሰዎችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት ማሸጋገር ያስቻለው የከተማ ግብርና

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በከተማ ግብርና ዘርፍ በተከናወኑ ውጤታማ ተግባራት በርካቶችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት ማሸጋገር መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ኮሚሽን አስታወቀ።

ባለፉት ዓመታት በተሰሩ ስራዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የከተማ ግብርና ቤተሰብ መፍጠር መቻሉንም ጠቁሟል፡፡

በከተማ ግብርና እየተሳተፉ የሚገኙ ዜጎች በበኩላቸው፤ በዘርፉ በመሰማራታቸው ከዕለታዊ ፍጆታ ባለፈ ሌሎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን ይናገራሉ።

በከተማ ግብርና የተሰማሩ ዜጎች በበኩላቸው፤ ከራሳቸው ፍጆታ ባለፈ ለሌሎች ማኅበረሰብ ክፍሎች ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

የከተማ ግብርና ስትራቴጂዎች ሀገራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጉዞ፣ ዜጎች በራሳቸው አቅም ምግብን ማምረት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየና የሥራ ባህልን የቀየረ ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው፡፡

ይህ የተቀናጀ ጥረት ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በምግብ ራስን ለመቻልና ከድህነት ለመውጣት ለጀመረችው ጉዞ እንደ ትልቅ ስኬት የሚወሰድ ነው።


የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ባዩ ሽጉጤ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በከተማ ግብርና በተከናወኑ ተግባራት ዜጎችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመለወጥ ዘርፈ-ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በመዲናዋ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የሚገኙና ቀደም ሲል የሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚ የነበሩ የማኅበረሰብ ክፍሎች፣ ወደ አምራችነት እንዲሸጋገሩ መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡

ይህም በከተማ ግብርና አይቻልም የሚለውን የተሳሳተ አመለካከት በመቀየር፣ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የከተማ ግብርና ተጠቃሚ ቤተሰቦችን መፍጠር ማቻሉንም ጠቁመዋል፡፡

በተመሣሣይ ከሁለት ሺህ ሰባት መቶ በላይ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በተቀናጀ ሁኔታ በከተማ ግብርና ላይ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል።

በመዲናዋ በከተማ ግብርና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ያላቸውን ዜጎች ተጠቃሚ የማድረግ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በከተማ ግብርና በአነስተኛ ቦታ ላይ በማምረት ከራስ ፍጆታ አልፎ ለገበያ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርት ማቅረብ መጀመሩንም ጠቁመዋል።

በከተማ ግብርና እየተሳተፉ የሚገኙ ዜጎች በበኩላቸው፤ በዘርፉ በመሰማራታቸው ከዕለታዊ ፍጆታ ባለፈ ሌሎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻላቸውን ይናገራሉ።

ከአስተያየት ሰጪዎች መካከል ሸምሱ ነጋሽ፤ ቀደም ሲል በሴፍቲኔት ፕሮግራም ተረጂ እንደነበሩ አስታውሰው፣ መንግሥት ባመቻቸላቸው ዕድል ወደ ከተማ ግብርና በመግባት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ወይዘሮ መይሙና ጀማል በበኩላቸው፤ ቀደም ሲል ምንም ዓይነት የገቢ ምንጭ እንዳልነበራቸው አስታውሰው፤ አሁን በከተማ ግብርና ተሰማርተው ውጤታማ እየሆኑ መመጣታቸውን ተናግረዋል።


ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ወጣት ሽመልስ ድሪባ፤ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ከጓደኞቹ ጋር በመደራጀት ውጤታማ ሥራ እየሠራ መሆኑን ገልጿል።

ከመንግሥት ባገኙት ብድር አምስት ላሞች ገዝተው ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቅሶ በአሁኑ ወቅት የላሞቻቸው ቁጥር ከ20 በላይ መድረሱንና ለሌሎች ወጣቶችም የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ተናግሯል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026