የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በከተሞች ከ200 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠሩ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ ነው

Jun 5, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ግንቦት 28/2018( ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በከተሞች ከ200 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠሩ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ ከተሞችን በኮሪደር ልማት ኢንሼቲቭ የማዘመን፣በቴክኖሎጂ የማላቅና ስማርት የማድረግ ስራ በሰፊው እየተካሄደ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።

የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፥ በክልሉ ከተሞችን ለኑሮና ኢንቨስትመንት ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።

ለዚህም በተለያዩ ከተሞች ከ8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።

በከተሞቹ 1 ሺህ 10 የልማት ፕሮጀክቶች ተነድፈው በቅንጅት እየተተገበሩ መሆኑን አመልክተዋል።

የልማት ፕሮጀክቶቹ በከተማ አስተዳደሮች በጀትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ ግንባታቸው እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመው፥ በፕሮጀክቶቹ ግንባታ ከ200 ሺህ ለሚበልጡ ወገኖች የስራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።

ከፕሮጀክቶቹ መካከል እስካሁን በተደረገ ጥረት 336 የሚሆኑት ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃታቸውን ጠቅሰው፤ቀሪዎቹን እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ከእነዚሁ ፕሮጀክቶች መካከልም 14 ኪሎ ሜትር የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ መንገድ፣ ከ40 በላይ የተለያየ ደረጃ ያላቸው ድልድዮች፣ ከ80 በላይ ሼዶች እንዲሁም የኤሌክትሪክና የውሃ መስመር ዝርጋታና ሌሎች መሰረተ ልማቶች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

በመሰረተ ልማት ማስፋፋት ስራ የከተሞችን ሁለንተናዊ ገፅታ በመቀየር ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ መቻሉንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026