የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በከተሞች ከ200 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠሩ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ ነው

Jun 5, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ግንቦት 28/2018( ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በከተሞች ከ200 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠሩ የልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ ከተሞችን በኮሪደር ልማት ኢንሼቲቭ የማዘመን፣በቴክኖሎጂ የማላቅና ስማርት የማድረግ ስራ በሰፊው እየተካሄደ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።

የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፥ በክልሉ ከተሞችን ለኑሮና ኢንቨስትመንት ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።

ለዚህም በተለያዩ ከተሞች ከ8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።

በከተሞቹ 1 ሺህ 10 የልማት ፕሮጀክቶች ተነድፈው በቅንጅት እየተተገበሩ መሆኑን አመልክተዋል።

የልማት ፕሮጀክቶቹ በከተማ አስተዳደሮች በጀትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ ግንባታቸው እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመው፥ በፕሮጀክቶቹ ግንባታ ከ200 ሺህ ለሚበልጡ ወገኖች የስራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረዋል።

ከፕሮጀክቶቹ መካከል እስካሁን በተደረገ ጥረት 336 የሚሆኑት ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃታቸውን ጠቅሰው፤ቀሪዎቹን እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ከእነዚሁ ፕሮጀክቶች መካከልም 14 ኪሎ ሜትር የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ መንገድ፣ ከ40 በላይ የተለያየ ደረጃ ያላቸው ድልድዮች፣ ከ80 በላይ ሼዶች እንዲሁም የኤሌክትሪክና የውሃ መስመር ዝርጋታና ሌሎች መሰረተ ልማቶች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

በመሰረተ ልማት ማስፋፋት ስራ የከተሞችን ሁለንተናዊ ገፅታ በመቀየር ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ መቻሉንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026