🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018(ኢዜአ)፦የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወልድያ ከተማ ሰፊ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በምሽት ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)፤ ወልድያ በርካታ ከተሞችን የምታገናኝ በመሆኗ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቱ ስትራቴጂካዊ እሴቷን ከፍ እንዳደረገው ገልጸዋል።
ቀደም ሲል የነበሩ ጎስቋላና ጠባብ ስፍራዎች ተወግደው፣ ምቹ ድልድዮችና ሰፋፊ የመዝናኛና የንግድ ቦታዎች ተከፍተዋል ነው ያሉት።

ኮሪደር ልማት ከውበት የዘለለ የትውልድና የሀገር ግንባታ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፥ዛሬ በእነዚህ መንገዶች ላይ የሚንሸራሸሩ ህጻናት ነገ ሀገር የሚረከቡ በመሆናቸው ስራው ትውልድ ተሻጋሪ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል።
የክልሉ ከተሞች ከወልድያ የፈጠራና የሀብት ቁጠባ ተሞክሮ ሊማሩ እንደሚገባ ተናግረዋል።
የአማራ ክልል የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት በክልሉ በሚገኙ 43 ከተሞች ውስጥ ማዘጋጃ ቤቶችን ጨምሮ የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴ በስፋት እየተካሄደ ይገኛል።
የክልሉ ከተሞች ከጎስቋላ ገፅታ ተላቀው ምቹ የሥራ፣ የመኖሪያና የቱሪዝም ሥፍራ እየሆኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

ወልድያ ከተማ በከፍተኛ ፍጥነትና በጥራት በመስራት አስደናቂ ለውጥ ማምጣቷን ገልጸዋል።
የከተማዋን ልማት ውስን ሀብትን በቁጠባና በጥራት የመጠቀምና ብዙ ሥራዎችን በፍጥነት የማሳካት ጥበብ በመከተል የመደመር መንግሥት ኢንተርፕረኒያል እሳቤን እየተገበረች መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው አብራርተዋል።
የወልድያ አመራርና ህዝብ ከተማችን ተጎሳቁላ አትኖርም በሚል የጋራ መግባባት ፈጥረው፣ ሀብት አሰባስበውና ፈጣን እርምጃ ወስደው የከተማዋን የኢኮኖሚ እሴት ከፍ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።
ይህም አመራር ከሕዝብ ጋር ተቀናጅቶ ከሠራ ማንኛውንም ተግዳሮት ማሸነፍ እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫና ለክልሉም ትምህርት የሚሰጥ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026