የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ የሳይንስና የፈጠራ ሥራዎችን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቡታጅራ፤ ሰኔ 5/2018 (ኢዜአ፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ችግር ፈቺ የሳይንስና የፈጠራ ሥራዎችን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ ገለጹ፡፡

"የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን የሳይንስ፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ" በሚል መሪ ሀሳብ በቡታጅራ ከተማ 3ኛው ዙር ክልላዊ የሳይንስና የፈጠራ ሥራዎች አውደ ርዕይ ተከፍቷል።


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ የሳይንስና የፈጠራ ሥራዎችን ለማሳደግ ትኩረት ተጥቷል፡፡

በክልሉ የሚካሄደው የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂና የፈጠራ አውደ ርዕይም በዘርፉ ተሰጥኦ ያላቸው የፈጠራ ባለቤቶችን በማበረታታት ከክልሉ አልፎ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት የመደመር መንግስት እሳቤ ለሳይንስ፣ ለቴክኖሎጂና ለፈጠራ ሥራዎች መስፋፋት መሰረት ጥሏል።

በዚህም የዘርፉን አቅም ወደ ሀብት መቀየር የሚችሉ የፖሊሲና የህግ ማሻሻያዎች ሲደረጉ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በፈጠራ ሥራዎች ሁሉንም ዜጋ ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ዝርጋታ መከናወኑንም ጠቁመዋል።


ለሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ትግበራው ስኬታማነት ጥራቱን የጠበቀ የትምህርት ስርዓት ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ደግሞ በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ናቸው።

ለዚህም አዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ ለሳይንስ፣ ለምርምር፣ ለእውቀት ሽግግር፣ ለቴክኖሎጂና ለኢንዱስትሪ ትስስር፣ ለኢንተፕራይዞች ልማት መስፋፋትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ጠቁመዋል።

የመማር ማስተማር ስራውን ከተለመደው አሰራር በማውጣት በዲጅታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግም የዚሁ አስቻይ ሁኔታ አካል መሆኑንም ገልጸዋል።

በአውደ ርዕዩ የአፈር ለምነትን በማሳደግ ምርትና ምርታማነት መጨመር የሚያስችል የተፈጥሮ ማዳበሪያ የምርምር ውጤት ይዘው መቅረባቸውን የተናገሩት ደግሞ መምህር ታምራት ተስፋዬ ናቸው።

የአውደ ርዕዩ መዘጋጀት የምርምር ስራቸውን እንዲያስተዋውቁና ወደ ገበያ በማውጣት ለውጤታማነታቸው ተጨማሪ አቅም እንደሚሆናቸው ተናግረዋል።


ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ክልል አቀፍ የሳይንስ፣ ኢኖቬሽንና የፈጠራ ሥራዎች አውደ ርዕይ የፈጠራ ሥራዎችን ከማስተዋወቅ ባለፈ ለተሻሉት እውቅናና ሽልማት እንደሚሰጥ ታውቋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የፌዴራል፣ የክልሉና የምስራቅ ጉራጌ ዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የፈጠራ ባለቤቶችና ተማሪዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026