የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በምዕራብ ሸዋ ዞን በ960 ሄክታር መሬት ላይ የምርጥ ዘር ብዜት እየተከናወነ ነው

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አምቦ፤ ሰኔ 7/2018 (ኢዜአ) ፡-በምዕራብ ሸዋ ዞን በዘንድሮው የመኸር ወቅት የምርጥ ዘር አቅርቦትን በራስ አቅም ለመሸፈን በ960 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ ምርጥ ዘሮችን የማባዛት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

ምዕራብ ሸዋ ዞን በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ካሉ ዋና ዋና የሰብል አምራች አካባቢዎች አንዱ ሲሆን፥ በተለይም እንደ ስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍ እና ጥራጥሬዎች በስፋት ይመረቱበታል።

የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት በየዓመቱ የምርታማነት መጠንን ለመጨመር ዘመናዊ የግብርና ግብዓቶችን ተደራሽ ለማድረግ ይሰራል።

በዞኑ የተጀመረው በ960 ሄክታር መሬት ላይ ምርጥ ዘርን የማባዛት ሥራ፥ ቀደም ሲል የነበረውን እጥረት በማስቀረት ዞኑ በምርጥ ዘር አቅርቦት ራሱን እንዲችል ለማድረግ ያለመ ነው።

ይህ ስትራቴጂ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የአፈር ዓይነቶችንና የአየር ንብረትን መነሻ በማድረግ የተመረጡና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የሰብል ዝርያዎችን በአካባቢው አባዝቶ በቀጥታ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ያስችላል።

የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት የግብርና ሜካናይዜሽንና ግብዓት አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ዘሪሁን ጌትነት ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በተሻሻሉ ምርጥ ዘሮች ብዜትና ማስፋፋት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሠራ ነው።

በዞኑ በመኸር ወቅቱ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡና በሽታን መቋቋም የሚችሉ የምርጥ ዘር ዝርያዎችን በ960 ሄክታር ማሳ ላይ በማባዛት 24 ሺህ 200 ኩንታል ምርጥ ዘር ለማግኘት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ገልጸዋል።

ከእነዚህም መካከል በቆሎ፣ ስንዴ፣ ጤፍ እና ሌሎች ሰብሎች እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።

እስካሁን ባለው ሂደት ከ130 ሄክታር በላይ ማሳ በበቆሎ ምርጥ ዘር መሸፈኑን የገለጹት አቶ ዘሪሁን፤ አርሶ አደሮቹ የግብርና ግብዓቶችንና የኤክስቴንሽን አሰራሮችን በተግባር እያዋሉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የምርጥ ዘር ብዜቱ በደንዲ፣ ኢሉ ገላን እና ባኮ ቲቤ ወረዳዎች በሚገኙ የገበሬዎች ሕብረት ሥራ ዩኒየኖችና በሞዴል አርሶ አደሮች ማሳ ላይ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በዘር ብዜት ሥራው ላይ ከ2 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ ሲሆን፣ ለሥራው ውጤታማነት ለአርሶ አደሮቹ ሥልጠና ከመስጠት ባለፈ ጽሕፈት ቤቱ በቅርበት የቴክኒክ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ የዘር ብዜት ሥራ የአርሶ አደሩን የምርጥ ዘር እጥረት ከመቅረፍ ባለፈ፣ ለገበያ የሚቀርብ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ እንደሚሆንም አቶ ዘሪሁን አስረድተዋል።

በምዕራብ ሸዋ ዞን በዘንድሮው የመኸር እርሻ በአጠቃላይ ከ900 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች እየለማ እንደሚገኝ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026