የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል

Jun 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዱራሜ ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ የዱራሜ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ የመንግስት አገልግሎትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአንድ ቋት የተለያዩ አገልግሎቶችን በመስጠት የማህበረሰቡን ጊዜና ጉልበት ከመቆጠብ በተጨማሪ ብልሹ አሰራርን በመከላከል ረገድ በጎ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።


በክልሉ በሚገኙ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት ተገንብተው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው በዱራሜ ዛሬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው 6ኛው መሆኑን ጠቅሰዋል።

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ በበኩላቸው፤ የመንግስት አገልግሎትን በማዘመን ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ የማድረግ ስራ በልዩ ትኩረት እየተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል።


አገልግሎቱን በሌሎች መዋቅሮች በማስፋት የማህበረሰቡን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አመላክተዋል።

የዱራሜ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ነፃነት አፌቦ፤ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል በመንግስታዊ አገልግሎቶች ላይ ይስተዋል የነበረን የአሰራር ችግር ይቀርፋል የሚል እምነት እንዳላቸው አመላክተዋል።በማእከሉ ስራ መጀመር መደሰታቸውንም ገልጸዋል።


መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ አገልግሎቶችን በአንድ ቋት በመሰብሰብ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑ እንግልትን ያስቀራል ያሉት ደግሞ የከተማው ነዋሪ አቶ በየነ አርፊጮ ናቸው።

በስነ ስርአቱ ላይ የክልል ፣ የዞንና የዱራሜ ከተማ ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026