የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል

Jun 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ዱራሜ ፤ ሰኔ 19/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለፁ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ የዱራሜ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ የመንግስት አገልግሎትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ተግባራት ይጠናከራሉ።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአንድ ቋት የተለያዩ አገልግሎቶችን በመስጠት የማህበረሰቡን ጊዜና ጉልበት ከመቆጠብ በተጨማሪ ብልሹ አሰራርን በመከላከል ረገድ በጎ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።


በክልሉ በሚገኙ ከተሞች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት ተገንብተው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው በዱራሜ ዛሬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው 6ኛው መሆኑን ጠቅሰዋል።

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ በበኩላቸው፤ የመንግስት አገልግሎትን በማዘመን ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ የማድረግ ስራ በልዩ ትኩረት እየተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል።


አገልግሎቱን በሌሎች መዋቅሮች በማስፋት የማህበረሰቡን እርካታ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አመላክተዋል።

የዱራሜ ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ነፃነት አፌቦ፤ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል በመንግስታዊ አገልግሎቶች ላይ ይስተዋል የነበረን የአሰራር ችግር ይቀርፋል የሚል እምነት እንዳላቸው አመላክተዋል።በማእከሉ ስራ መጀመር መደሰታቸውንም ገልጸዋል።


መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ አገልግሎቶችን በአንድ ቋት በመሰብሰብ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑ እንግልትን ያስቀራል ያሉት ደግሞ የከተማው ነዋሪ አቶ በየነ አርፊጮ ናቸው።

በስነ ስርአቱ ላይ የክልል ፣ የዞንና የዱራሜ ከተማ ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026