🔇Unmute
አርባ ምንጭ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ በከተማና መሠረተ ልማት ዘርፍ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ አበይት ተግባራት መከናወናቸውን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ አስታወቁ።
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማን በአርባ ምንጭ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።

ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ፤ መንግሥት ለከተሞች ዕድገትና መስፋፋት እንዲሁም ለዜጎች ሕይወት መቃናት በልዩ ትኩረት እየሠራ በመሆኑ፣ ዘመኑ የከተሞች የትንሣኤ ዘመን ነው ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ በተቋማዊ የማስፈጸም አቅም፣ በሀብት አጠቃቀም እና በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ሰፊ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንም ገልጸዋል።
ከተሞችን የብልጽግና ተምሳሌት ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ የሥራ ባሕላችንን በመቀየር ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ተችሏልም ነው ያሉት።
ከዚህም ባለፈ በከተሞች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥራዎች መሠራታቸውን ገልጸው፤ በቤቶች ልማት ዘርፍም ሰፊ ለውጥ እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል።
በቀጣይም ከተሞች ከድህነት፣ ከጉስቁልና፣ ከሥራ አጥነት እና ከመልካም አስተዳደር ችግሮች ወጥተው፣ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ እንዲፋጠን በትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል።

የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ከተማዋ ባላት የተፈጥሮ ጸጋ ልክ ለማደግ ሩቅ አልማ እየተጋች መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም ቱሪዝምን የልሕቀት ማዕከል ባደረገ መልኩ መጠነ ሰፊ ልማቶች እየተከናወኑ ሲሆን፣ የኮሪደር ልማቱም የከተማዋን ተወዳዳሪነትና ውበት ይበልጥ ገልጦ እያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚሁ የአፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ፣ የፌዴራልና የክልል እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...
Jun 24, 2026
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026