የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በከተማና መሠረተ ልማት ዘርፍ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ በከተማና መሠረተ ልማት ዘርፍ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ አበይት ተግባራት መከናወናቸውን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ አስታወቁ።

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማን በአርባ ምንጭ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።


ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ፤ መንግሥት ለከተሞች ዕድገትና መስፋፋት እንዲሁም ለዜጎች ሕይወት መቃናት በልዩ ትኩረት እየሠራ በመሆኑ፣ ዘመኑ የከተሞች የትንሣኤ ዘመን ነው ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በተቋማዊ የማስፈጸም አቅም፣ በሀብት አጠቃቀም እና በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ሰፊ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንም ገልጸዋል።

ከተሞችን የብልጽግና ተምሳሌት ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ የሥራ ባሕላችንን በመቀየር ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ተችሏልም ነው ያሉት።

ከዚህም ባለፈ በከተሞች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥራዎች መሠራታቸውን ገልጸው፤ በቤቶች ልማት ዘርፍም ሰፊ ለውጥ እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል።

በቀጣይም ከተሞች ከድህነት፣ ከጉስቁልና፣ ከሥራ አጥነት እና ከመልካም አስተዳደር ችግሮች ወጥተው፣ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ እንዲፋጠን በትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል።


የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ከተማዋ ባላት የተፈጥሮ ጸጋ ልክ ለማደግ ሩቅ አልማ እየተጋች መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ቱሪዝምን የልሕቀት ማዕከል ባደረገ መልኩ መጠነ ሰፊ ልማቶች እየተከናወኑ ሲሆን፣ የኮሪደር ልማቱም የከተማዋን ተወዳዳሪነትና ውበት ይበልጥ ገልጦ እያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዚሁ የአፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ፣ የፌዴራልና የክልል እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026