የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በከተማና መሠረተ ልማት ዘርፍ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራት ተከናውነዋል

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ በከተማና መሠረተ ልማት ዘርፍ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ አበይት ተግባራት መከናወናቸውን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ አስታወቁ።

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማን በአርባ ምንጭ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።


ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ፤ መንግሥት ለከተሞች ዕድገትና መስፋፋት እንዲሁም ለዜጎች ሕይወት መቃናት በልዩ ትኩረት እየሠራ በመሆኑ፣ ዘመኑ የከተሞች የትንሣኤ ዘመን ነው ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በተቋማዊ የማስፈጸም አቅም፣ በሀብት አጠቃቀም እና በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ሰፊ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንም ገልጸዋል።

ከተሞችን የብልጽግና ተምሳሌት ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ የሥራ ባሕላችንን በመቀየር ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ተችሏልም ነው ያሉት።

ከዚህም ባለፈ በከተሞች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥራዎች መሠራታቸውን ገልጸው፤ በቤቶች ልማት ዘርፍም ሰፊ ለውጥ እየተመዘገበ ይገኛል ብለዋል።

በቀጣይም ከተሞች ከድህነት፣ ከጉስቁልና፣ ከሥራ አጥነት እና ከመልካም አስተዳደር ችግሮች ወጥተው፣ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ እንዲፋጠን በትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል።


የአርባ ምንጭ ከተማ ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ከተማዋ ባላት የተፈጥሮ ጸጋ ልክ ለማደግ ሩቅ አልማ እየተጋች መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም ቱሪዝምን የልሕቀት ማዕከል ባደረገ መልኩ መጠነ ሰፊ ልማቶች እየተከናወኑ ሲሆን፣ የኮሪደር ልማቱም የከተማዋን ተወዳዳሪነትና ውበት ይበልጥ ገልጦ እያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል።

በዚሁ የአፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ፣ የፌዴራልና የክልል እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026