የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማት ከሐይቁ የተፈጥሮ ውበት ጋር ተሰናስሎ በልዩ ዲዛይን በላቀ ጥራት እየተገነባ ነው

Jul 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

‎ሀዋሳ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):-የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማት ከሐይቁ የተፈጥሮ ውበት ጋር ተሰናስሎ በልዩ ዲዛይን በላቀ ጥራት እየተገነባ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ።

የከተማዋ ነዋሪዎች በበኩላቸው ለከተማዋ የኮሪደርና የሐይቅ ዳርቻ ልማት ሥራዎች የሚጠበቅባቸውን በመወጣት ታሪካዊ አሻራቸውን እንደሚያሳርፉ ገልጸዋል።

ሀገራዊ የኮሪደር ልማት ኢኒሺዬቲቭ መተግበር ከተጀመረ በኋላ ከተሞች ውብ ገፅታና ዘመናዊነትን ከመላበስ ባለፈ ለኑሮና ለንግድ እንቅስቃሴ ምቹ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡

በሃዋሳ ከተማ ደግሞ ልማቱ ከተማዋ የቱሪስት መዳረሻነቷ ከፍ እንዲል፣ ለኑሮም ምቹ እንድትሆንና ውበቷም ይበልጥ እንዲጎላ እያደረጋት ነው።


በቅርቡም ከኮሪደር ልማቱ በተጨማሪ የተፈጥሮ ጸጋዎቿ እንዲገለጡ የሚያደርግና ከኮሪደር ጋር የተሰናሰለ የሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ተጀምሯል፡፡

ፕሮጀክቱን በማስመልከት ኢዜአ ያነጋገራቸው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ እንዳሉት፤ የሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማት ከሐይቁ የተፈጥሮ ውበት ጋር ተሰናስሎ በልዩ ዲዛይን በላቀ ጥራት እየተከናወነ ነው።

የሐይቅ ዳርቻ ልማቱ የከተማዋን የኮንፈረንስ ማዕከልነት እንዲሁም የጎብኚዎቿን የቆይታ ጊዜ እንደሚያራዝመው አንስተዋል፡፡

ፕሮጀክቱ የማህበረሰቡ አሻራ በጉልህ እንዲያርፍ ታስቦ መጀመሩን የገለጹት ከንቲባው 3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በጀት እንደተያዘለትና ህብረተሰቡም በአቅሙ አስተዋጽኦ በማድረግ የድርሻውን እንዲወጣ አመልክተዋል።

እንደ ከንቲባ ጥራቱ ገለጻ፤ በከተማዋ በ2ኛ እና በ3ኛ ዙር 8 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ ተከናውኗል።

ልማቱም የብስክሌት፣ የሞተር ብስክሌትና የመኪና ማቆሚያዎች፣ የታክሲ መጫኛና ማውረጃ፣ የሕፃናት መጫወቻዎችንና የወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያዎች አካቶ የተከናወነ መሆኑንም አመልክተዋል።

በአሁን ወቅት 4 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው አራተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ ልማቱም ከሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ጋር መሰናሰሉን አመልክተዋል።

የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች በበኩላቸው፤ በከተማዋ እየተከናወኑ ባሉ የኮሪደርና የሐይቅ ዳርቻ ልማት ሥራዎች የሚጠበቅባቸውን በመወጣት ታሪካዊ አሻራቸውን እንደሚያሳርፉ አረጋግጠዋል።


ከነዋሪዎቹ መካከል ወይዘሮ ያምሮት ኃይሌ የኮሪደር ልማቱ ሀዋሳ ድሮ ከነበራት ውበት በላይ እንዳደመቃትና ተወዳዳሪ እንዳደረጋት ተናግረዋል።

በሆቴል ሥራ ዘርፍ የተሰማሩት አቶ ለገሰ ላሚሶ በበኩላቸው፤ በከተማዋ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ በተለይ የሆቴል ዘርፉ እንዲነቃቃ የጎላ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።


ወደ ሀዋሳ የሚመጡ እንግዶችን በላቀ መስተንግዶ ተቀብለው ለማስተናገድ ይበልጥ መነቃቃታቸውን ገልጸው፣ የተጀመረው የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ተጠናቆ ከተማዋ ይበልጥ እንድታድግ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026