የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የምርጥ ዘር አቅርቦትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቷል

Jul 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ሰኔ 25/2018(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምርጥ ዘር አቅርቦትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማረጋገጥ ትኩረት መስጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡


የክልሉ ምርጥ ዘር ድርጅት በአሪ ዞን በደቡብ አሪ ወረዳ ጨለጎድ ቀበሌ ለምርጥ ዘር ብዜት የሚውል 1 ሺህ ሄክታር መሬት ተረክቧል።


የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ በወቅቱ እንደገለፁት፤ በክልሉ ግብርናውን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል ለምርጥ ዘር ብዜት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።


የምርጥ ዘር ብዜቱን በማስፋት የክልሉን ፍላጎት ከመሸፈን ባለፈ ለሌሎች ክልሎች ለመትረፍ የተጨማሪ መሬት ርክክብ መከናወኑን ገልጸዋል።


በክልሉ የምርጥ ዘር አቅርቦትን በማሻሻል የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን ያመለከቱት ደግሞ የክልሉ ምርጥ ዘር ድርጅት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ግዛው ናቸው።


ድርጅቱ በተለያዩ ማዕከላትና በአርሶ አደሮች ማሳ ላይ ምርጥ ዘር እያለማ መሆኑን አንስተው፤ ዛሬ ርክክብ የተደረገው መሬትም በቀጣይ የምርጥ ዘር አቅርቦት ሽፋኑን ለማሳደግ እየተደረገ ላለው ጥረት ትልቅ አጋዥ መሆኑን ገልጸዋል።


የአሪ ዞን አስተዳደር ተወካይ አቶ አፌዶ ወርቁ በበኩላቸው፤ በክልሉ የተጀመረው የምርጥ ዘር ብዜት ንቅናቄ በዞኑ ያለውን የምርጥ ዘር አቅርቦት እንደሚያሰፋው ጠቅሰዋል።


ዛሬ ርክክብ የተካሄደበት መሬትም የግብርና ቴክኖሎጂ ሽግግርን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነትና የስራ ዕድል ፈጠራን የሚያጠናክር መሆኑን ጠቁመዋል።


በወረዳው በደጋማ አካባቢዎች የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት በአርሶ አደር ማሳና በኮርፖሬት ኢንቨስትመንት በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የደቡብ አሪ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ደኢዶቆ ናቸው።


በዚህ የምርጥ ዘር ብዜት መሬት ርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026