የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የምርጥ ዘር አቅርቦትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቷል

Jul 3, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ሰኔ 25/2018(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምርጥ ዘር አቅርቦትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማረጋገጥ ትኩረት መስጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡


የክልሉ ምርጥ ዘር ድርጅት በአሪ ዞን በደቡብ አሪ ወረዳ ጨለጎድ ቀበሌ ለምርጥ ዘር ብዜት የሚውል 1 ሺህ ሄክታር መሬት ተረክቧል።


የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ግዳልቅ አልቅሚ በወቅቱ እንደገለፁት፤ በክልሉ ግብርናውን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል ለምርጥ ዘር ብዜት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።


የምርጥ ዘር ብዜቱን በማስፋት የክልሉን ፍላጎት ከመሸፈን ባለፈ ለሌሎች ክልሎች ለመትረፍ የተጨማሪ መሬት ርክክብ መከናወኑን ገልጸዋል።


በክልሉ የምርጥ ዘር አቅርቦትን በማሻሻል የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን ያመለከቱት ደግሞ የክልሉ ምርጥ ዘር ድርጅት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ግዛው ናቸው።


ድርጅቱ በተለያዩ ማዕከላትና በአርሶ አደሮች ማሳ ላይ ምርጥ ዘር እያለማ መሆኑን አንስተው፤ ዛሬ ርክክብ የተደረገው መሬትም በቀጣይ የምርጥ ዘር አቅርቦት ሽፋኑን ለማሳደግ እየተደረገ ላለው ጥረት ትልቅ አጋዥ መሆኑን ገልጸዋል።


የአሪ ዞን አስተዳደር ተወካይ አቶ አፌዶ ወርቁ በበኩላቸው፤ በክልሉ የተጀመረው የምርጥ ዘር ብዜት ንቅናቄ በዞኑ ያለውን የምርጥ ዘር አቅርቦት እንደሚያሰፋው ጠቅሰዋል።


ዛሬ ርክክብ የተካሄደበት መሬትም የግብርና ቴክኖሎጂ ሽግግርን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነትና የስራ ዕድል ፈጠራን የሚያጠናክር መሆኑን ጠቁመዋል።


በወረዳው በደጋማ አካባቢዎች የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት በአርሶ አደር ማሳና በኮርፖሬት ኢንቨስትመንት በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ የተናገሩት ደግሞ የደቡብ አሪ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ደኢዶቆ ናቸው።


በዚህ የምርጥ ዘር ብዜት መሬት ርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የክልል፣ የዞንና የወረዳ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026