የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በዞኑ የግብርናውን ዘርፍ በሜካናይዜሽን በመደገፍ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ትልቅ ለውጥ እየታየ ነው

Jul 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ፤ ሰኔ 27/2018 (ኢዜአ)፦ በባሌ ዞን የግብርናውን ዘርፍ በሜካናይዜሽን በመደገፍ የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ረገድ ትልቅ ለውጥ እየታየ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱልሀኪም አልይ አመለከቱ።

አርሶ አደሩ የተሻሻሉ አሰራሮችና ቴክኖሎጂዎችን የመጠቀም ዝንባሌና ተግባር እየተሻሻለ መምጣት ለምርትና ምርታማነቱ ማደግ ተጠቃሽ መሆኑ ተመላክቷል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱልሀኪም አልይ በተለይ ለኢዜአ እንዳሉት ፤መንግስት የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት በማሻሻል የምግብ ዋስትናውን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ነው።


ለአብነትም በበልግ እርሻ ከ256 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት ላይ የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ በተለያዩ የሰብል ዘሮች ማልማት መቻሉን አመልክተዋል።

አርሶ አደሩ የግብርና ሜካናይዜሽንና ሌሎች የተሻሻሉ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ 80 በመቶ የሚሆነውን መሬት ማልማት መቻላቸውን አመልክተዋል።

በአሁኑ ወቅት የአርሶ አደሩ የሜካናይዜሽንና የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ነው የጠቆሙት።

ይሕም በአንድ ሄክታር መሬት የስንዴ ማሳ በአማካይ ይመረት የነበረውን ከ20 ኩንታል የማይበልጥ ምርት ከ60 እስከ 70 ኩንታል ማምረት እንደተቻለም ነው የገለጹት።

ለምርትና ምርታማነት መጨመር ዋነኛው ምክንያት የግብርና ሜካናይዜሽንን በማስፋት የተከናወኑ ተግባራት ትልቁን ፋይዳ ማበርከታቸውን ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ቀደም የዞኑ አርሶ አደሮች ትራክተርን ጨምሮ ሌሎች የግብርና ማሽነሪዎችን በብድር እንኳ ማግኘት ያዳግታቸው እንደነበር ነው ያስታወቁት፡፡

በአሁኑ ወቅት ግን አርሶ አደሩ የግብርና ማሽነሪዎችን ከቀረጥ ነጻ በብድር እንዲያገኝ መንግስት ከፍተኛ ስራ መስራቱን አስተዳዳሪው ተናግረዋል፡፡


በዞኑ በዝናብ ብቻ ሁለት ጊዜ የማምረት ፀጋ መኖሩን ጠቅሰው፤ ከበልግ በተጨማሪ በመኽሩ የምርት ወቅት ከ538 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በተለያዩ የሰብል ዘሮች የማልማት አቅም መፈጠሩን አክለዋል።

ከዚህም ከ17 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት የመሰብሰብ አቅም መፈጠሩን ገልፀዋል።

በዞኑ በዝናብ ውኃ ከሚለማው እርሻ ባሻገር የተለያዩ የውኃ አማራጮችን በመጠቀም ከ170 ሺህ ሄክታር መሬት በመስኖ አማራጭ ማልማት መቻሉን ጠቁመዋል።

ከ 6 ሚሊዮን ኩንታል ባላይ ምርት መሰብሰብ እንደተቻለም ነው ዋና አስተዳዳሪው የገለጹት።

የአርሶ አደሩን የግብርና ሜካናይዜሽንና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ይበልጥ በማሻሻል ምርትና ምርታማነት በማሳደግ የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ወደ አዲስ ምእራፍ ለማሸጋገር ለሚደረገው ሀገራዊ ግብ ስኬት ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግም ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026