የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በዞኑ የአቮካዶ ዓመታዊ የምርት መጠን ከነበረበት 600 ኩንታል ወደ 2 ሚሊዮን ኩንታል አድጓል

Jul 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ ፤ ሐምሌ 3/ 2018 (ኢዜአ):- በኢሉባቦር ዞን ለአቮካዶ ልማት በተሰጠው ትኩረት፣ ዓመታዊ የምርት መጠኑን ከነበረበት 600 ኩንታል ወደ 2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማሳደግ መቻሉን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።

በኢሉባቦር ዞን ቀደም ሲል የነበረው የአቮካዶ አመራረት በአብዛኛው ልማዳዊ፣ ለረጅም ዓመታት ምርት የማይሰጥና በበሽታዎች የሚጠቃ በመሆኑ አርሶ አደሩ ከዘርፉ የሚያገኘው ጥቅም አነስተኛ ነበር።

ይህንን ክፍተት ለመሙላት የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ባለፉት ጥቂት ዓመታት በሽታን የሚቋቋሙ፣ ፈጣንና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የተሻሻሉ የአቮካዶ ዝርያዎችን የማባዛትና የማስተዋወቅ ስራ በስፋት ሲያከናውን ቆይቷል።


አርሶ አደሩም ከባህላዊ አሰራር ወጥቶ ዘመናዊ የኩትኳቶ፣ የውሃ አጠቃቀምና የክምችት አያያዝ ዘዴዎችን እንዲከተል መደረጉ ከፍተኛ የምርት እድገት እያስገኘ ነው።

የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኜ ፍቅሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የዞኑን ምቹ የአየር ንብረትና መልክዓ ምድር በመጠቀም፣ የአቮካዶ ልማት በልዩ ኢንሼቲቭ ተቀርጾ በኩታገጠም አሰራር በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።


ከአምስት ዓመታት በፊት በዞኑ ይመረት የነበረው ዓመታዊ የአቮካዶ ምርት ከ600 ኩንታል የማይበልጥ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ዳኜ፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ስራው በልዩ ኢንሼቲቭ መመራት ከጀመረ ወዲህ ግን የምርት መጠኑ በከፍተኛ ደረጃ አድጎ ከ2 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ሊሻገር መቻሉን ገልጸዋል።

ለዚህ ከፍተኛ የምርት ዕድገት ዋነኛው ምክንያት በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርት መስጠት የሚችሉ የተሻሻሉ የአቮካዶ ዝርያዎች ለአርሶ አደሩ በስፋት መሰራጨታቸው መሆኑን ምክትል ኃላፊው አብራርተዋል።

መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት በዞኑ የአቮካዶ ልማት መሬት ስፋት ከነበረበት 500 ሄክታር በአሁኑ ወቅት ወደ 54 ሺህ ሄክታር ማደጉንም ምክትል ኃላፊው ገልጸዋል።

ይህንኑ የልማት ተግባር አጠናክሮ ለማስቀጠል በዞኑ በሚገኙ ሰባት ወረዳዎች ላይ በተለየ ሁኔታ የማስፋፋት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ዳኜ፤ በአሁኑ ክረምትም 5 ሺህ 900 ሄክታር መሬት ላይ የአቮካዶ ችግኝ በኩታ ገጠም አሰራር የሚተከል መሆኑን አስታውቀዋል።

በዞኑ በአቮካዶ ልማት ላይ ከተሰማሩት የበቾ ወረዳ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ይማም ዓለሙ፤ ከልማቱ ተጨማሪ ገቢ ማግኘት መቻላቸውን ጠቅሰው፤ ይህም ለምግብ ዋስትና መረጋገጥና ለኑሮዋቸው መሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል።


በተመሳሳይ አርሶ አደር ተሾመ ጽጌ እና ድሪባ ገመቹ ፤ የተሻሻሉ የአቮካዶ ዝርያዎችን ማልማት ከጀመሩ ወዲህ የተሻለና ከፍተኛ ምርት ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል።

አርሶ አደሮቹ ከመደበኛ የእርሻ ሥራቸው ጎን ለጎን በአቮካዶ ልማት ላይ በመሳተፍ ተጨማሪ ገቢ ማግኘት መቻላቸውንና በዚህም ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

በኢሉባቦር ዞን በአሁኑ ወቅት ከ44 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በአቮካዶ ልማት ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ ከዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያሳያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026