🔇Unmute
ደሴ፤ ሐምሌ 4/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በመኸር እርሻ ከ60 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ኃላፊ ተገኝ አባተ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በዞኑ በ2018/19 የምርት ዘመን ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በዚህምበመኸር እርሻ 231 ሺህ 566 ሄክታር መሬት በማልማት ከሰባትሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ገልጸዋል።
የዝናቡ ወቅት ቀድሞ በጀመረባቸው አካባቢዎችእስካሁን ከ60 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን ማሳ በዘር መሸፈኑንም ነው ያመለከቱት።
አርሶ አደሩ የተሻሻሉ አሰራሮችንና ቴክኖሎጅዎችን እንዲጠቀም በማድረግ ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ከ160 ሺህ ኩንታል በላይ ዘመናዊ ማዳበሪያ መሰራጨቱን ነው የገለጹት።
የዝናብ መዘግየት ባለባቸው አካባቢዎችደግሞ የመስኖ አማራጭን በመጠቀም የመኸር ሰብል ልማቱን እንዲያከናውኑ ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በሰሜን ወሎ ዞን ባለፈው የመኸር ምርት ዘመን ከለማው 231ሺህ ሄክታር መሬት አምስትነጥብ ስምንት ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...
Jun 24, 2026
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026