የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአዲስ አበባ የተገነቡ የመንገድ መሠረተ ልማቶች ለትራፊክ ፍሰቱ መሳለጥ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው

Jul 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የተገነቡ የመንገድ መሠረተ ልማቶችና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ለትራፊክ ፍሰቱ መሳለጥ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ አስተያየታቸውን የሰጡ አሽከርካሪዎች ገለጹ።

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታ በማዘመን እና ዘመናዊ የመንገድ መሰረተ-ልማቶችን በመዘርጋት፣ የትራፊክ ፍሰትን ከማቀላጠፍ ባለፈ ለነዋሪዎች ምቹ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ቀልጣፋ አካባቢን መፍጠር አስችሏል፡፡

ሰፊና ደረጃቸውን የጠበቁ የእግረኛ መንገዶች በመገንባታቸው የከተማዋን ነዋሪዎች ሰላማዊ እንቅስቃሴ ከማረጋገጡም በላይ፣ የመንገድ ተጠቃሚዎችን ደህንነት በማስጠበቅ የትራፊክ አደጋዎችን ለመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።

አስተያየታቸውን የሰጡ አሽከርካሪዎች በከተማዋ የተሰሩት አዳዲስ መንገዶች እና የኮሪደር ልማት ስራዎች የትራፊክ ፍሰቱን በማሳለጥ አዎንታዊ ለውጥ አምጥተዋል ብለዋል።


አሽከርካሪ የሆኑት ኃይሌ ዘመድኩን እና ጤናዬ ጠንክር እንደገለጹት፤ የኮሪደር ልማቱ ለትራፊክ ፍሰት አመቺ እና ዘመናዊ መንገዶችን በመፍጠር ስጋት የለሽ የማሽከርከር ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል።

የከተማዋን ገጽታ በእጅጉ የቀየሩት እነዚህ ውብና ሰፋፊ መንገዶች፣ የዲዛይን ጥራታቸውና የተሟላ የመንገድ ምልክቶቻቸው ለትራፊክ አደጋ መቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ ብለዋል።


የኮሪደር ልማት ለከተማዋ ውበት ብቻ ሳይሆን፣ ለአሽከርካሪዎች የላቀ የደህንነት ስሜትና የጉዞ ቅልጥፍናን የሰጠ ስኬታማ የልማት ስራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አሽከርካሪ ብሩክ ግሩም፤ የኮሪደር ልማቱ የነበረውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ በመቅረፍ ተሽከርካሪዎች በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ በማድረጉ ጉዞን በአጭርና በአስተማማኝ ሁኔታ ማከናወን ተችሏል ብለዋል።


የመንገድ አቅም መጨመሩ ለትራፊክ ፍሰቱ መሻሻል ብቻ ሳይሆን፣ አደጋዎችን በእጅጉ በመቀነስ ለአሽከርካሪዎች ትልቅ የደህንነት እፎይታን የፈጠረ ውጤታማ የልማት ስራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ዘርጋ እንደገለጹት፤ የተከናወኑት የኮሪደር ልማት ስራዎች የትራፊክ ፍሰቱን በማቀላጠፍና የከተማዋን የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሰላማዊ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው።


ይህ ዘመናዊ የመንገድ አውታር እግረኞች በደህንነት ተጠብቀው በፍጥነት እንዲንቀሳቀሱ ምቹ ሁኔታን በመፍጠሩ፣ በያዝነው በጀት ዓመት በሰውና በንብረት ላይ ይደርስ የነበረውን የመንገድ አደጋ በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ ተችሏል ብለዋል።

ፕሮጀክቱ የመንገድ ደህንነትን በማረጋገጥና የትራፊክ መጨናነቅን በማስወገድ፣ በከተማዋ ለሚደረግ ማንኛውም አይነት የጉዞ እንቅስቃሴ አስተማማኝና ቀልጣፋ አማራጭ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026