የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአማራ ክልል ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል

Jul 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር ፤ ሐምሌ 6/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን የማረጋገጥ ስራ መከናወኑን የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ገለፀ።

በክልሉ ለስራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ ፀጋዎችን በመለየት ለወጣቶች የስራ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ አቅማቸውን የማሳደግ ስራ እየተሰራ ይገኛል።

የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ጎፋ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ለመፍጠር ተችሏል።


በዚሁ ወቅት የስራ እድል ፈጠራዉን ስኬታማ ለማድረግ በቅንጅት የሚመራ ግብረ ኃይል በማቋቋም እና አጋር ተቋማትን በማቀናጀት ሰፊ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል።

በዚህም ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የስራ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ መቻሉን ገልፀዋል።

ከተፈጠረው የስራ እድል ውስጥም 75 በመቶ በቋሚነት የተፈጠረ ሲሆን ከዚህ ውስጥም 50 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ነው የተናገሩት።

የስራ ዕድሉ በመስኖ እና በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣ በእንስሳት እርባታና ማድለብ፣ በጨርቃጨርቅና አልባሳት እንዲሁም በእንጨትና ብረታብረት ስራዎች የተፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚሁ ወቅት በስራ እድሉ ተጠቃሚ የሆኑ ዜጎች የገንዘብ እጥረት እንዳይገጥማቸው ለማድረግ በተከናወኑት ተግባራትም 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ከተለያዩ አበዳሪ ተቋማት እንዲያገኙ ተደርጓል ነው ያሉት።


በተጨማሪም 21 ሺህ 400 ሄክታር የሚጠጋ መሬትና ከ 2 ሺህ 200 የሚበልጡ የመስሪያና የመሸጫ ሼዶች ተገንብተው የስራ እድል ለተፈጠረላቸው ዜጎች ማስተላለፍ መቻሉን ገልፀዋል።

ኢንተርፕራይዞቹ የገበያ ትስስር ተጠቃሚ እንዲሆኑ በተከናወኑት ተግባራትም የ8 ነጥብ 3 ቢሊዮን የሀገር ውስጥ፤ ከ1 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ሃገራት የገበያ ትስስር መፈጠሩንም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026