የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአማራ ክልል ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል

Jul 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር ፤ ሐምሌ 6/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን የማረጋገጥ ስራ መከናወኑን የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ገለፀ።

በክልሉ ለስራ ዕድል ፈጠራ የሚያገለግሉ ፀጋዎችን በመለየት ለወጣቶች የስራ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ አቅማቸውን የማሳደግ ስራ እየተሰራ ይገኛል።

የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አንዳርጋቸው ጎፋ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በግብርና፣ በኢንዱስትሪና በአገልግሎት ዘርፎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ለመፍጠር ተችሏል።


በዚሁ ወቅት የስራ እድል ፈጠራዉን ስኬታማ ለማድረግ በቅንጅት የሚመራ ግብረ ኃይል በማቋቋም እና አጋር ተቋማትን በማቀናጀት ሰፊ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል።

በዚህም ከ1 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ወገኖች የስራ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ መቻሉን ገልፀዋል።

ከተፈጠረው የስራ እድል ውስጥም 75 በመቶ በቋሚነት የተፈጠረ ሲሆን ከዚህ ውስጥም 50 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ነው የተናገሩት።

የስራ ዕድሉ በመስኖ እና በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት፣ በእንስሳት እርባታና ማድለብ፣ በጨርቃጨርቅና አልባሳት እንዲሁም በእንጨትና ብረታብረት ስራዎች የተፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚሁ ወቅት በስራ እድሉ ተጠቃሚ የሆኑ ዜጎች የገንዘብ እጥረት እንዳይገጥማቸው ለማድረግ በተከናወኑት ተግባራትም 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ከተለያዩ አበዳሪ ተቋማት እንዲያገኙ ተደርጓል ነው ያሉት።


በተጨማሪም 21 ሺህ 400 ሄክታር የሚጠጋ መሬትና ከ 2 ሺህ 200 የሚበልጡ የመስሪያና የመሸጫ ሼዶች ተገንብተው የስራ እድል ለተፈጠረላቸው ዜጎች ማስተላለፍ መቻሉን ገልፀዋል።

ኢንተርፕራይዞቹ የገበያ ትስስር ተጠቃሚ እንዲሆኑ በተከናወኑት ተግባራትም የ8 ነጥብ 3 ቢሊዮን የሀገር ውስጥ፤ ከ1 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ሃገራት የገበያ ትስስር መፈጠሩንም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026