🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦የኮሪደር ልማቱ የባህርዳር ከተማን ውብና ጽዱ በማድረግ በቱሪዝም፣ በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ተመራጭና ተወዳዳሪ እንድትሆን ማድረጉን የባህርዳር ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ አስተዳደሩ ስራ አስኪያጅ አቶ ተሻገር አዳሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፣ የኮሪደር ልማቱ በጣና ሃይቅና አባይ ወንዝ የተከበበችውን ባህርዳር ከተማን ውበት ይበልጥ እንዲጎላ ያደረገ ነው።
ከተማ አስተዳደሩ በመጀመሪያውና በሁለተኛው ምእራፍ የኮሪደር ልማት ስምንት ነጥብ ስድስት ኪ.ሜ የሚሆን ስራ ማጠናቀቅ መቻሉን ገልጸዋል።
ደረጃቸውን የጠበቁ የሳይክልና የእግረኛ መንገዶች፣ የመንገድ ዳር ማረፊያዎች፣ መብራቶች ፣ፋውንቴኖችና ሌሎች የአረንጓዴ መዝናኛ ስፍራዎችን አካቶ መገንባቱ ከተማዋን ሳቢ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል።
በአሁኑ ወቅትም የሶስተኛው ምእራፍ የኮሪደር ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን ከተማዋን ይበልጥ ውብና ተመራጭነት ይበልጥ የሚያሳድግ እንደሆነም ነው የገለጹት።
ልማቱ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፎች ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ የአካባቢውን ኢኮኖሚ ማነቃቃት ያስቻለ መሆኑን አስረድተዋል።
በተጨማሪም በከተማዋ ዘመናዊ የአኗኗር ስርዓት ግንባታን በማፋጠን እና የስራ ባህልን በመቀየር ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስገንዝበዋል።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በኮሪደር ልማት ስራው ለ32 ሺህ ወጣቶች ሰፊ የስራ እድል መፍጠር መቻሉንም ነው ያመለከቱት።
ህብረተሰቡም ይዞታውን በነጻ በመልቀቅ፣ በጉልበትና በሀሳብ ካደረገው ተሳትፎ በተጨማሪ ከ500 ሚሊየን ብር በላይ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስገንዝበዋል።
የኮሪደር ልማቱ በፈረቃና በቅንጅት በመስራት የስራ ባህልን በመለወጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርከቷል ያሉት ደግሞ የኮሪደር ልማቱ ተቋራጪ ሳይት መሀንዲስ ዳሪክ ተስፋዬ ናቸው።

በኮሪደር ልማቱ በቫዞላ ንጣፍ ስራ የተሰማራው ወጣት ምሳው የኋላው በበኩሉ፤ የኮሪደር ልማቱ በከተማዋ እድገትና ዘመናዊነት ላይ የራሴን አሻራ እንዳሳርፍ አድርጎኛል ነው ያለው።
ልማቱ በፈጠረላቸው የስራ እድልም ገቢያቸውን በማሳደግ ከራሳቸው አልፎ ሌሎችንም ተጠቃሚ ለማድረግ መቻላቸውን ገልጿል።

በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች በስፋት እየተካሄደ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ የከተሞችን እድገት በማፋጠን በመሰረታዊነት ለውጥ እያመጣ መሆኑ ተመላክቷል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...
Jun 24, 2026
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026