የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የጥምቀት በዓልን ለማክበር ወደ ጎንደር የሚመጡ ቱሪስቶች ፓርኩን እንዲጎበኙ ዝግጅት ተደርጓል</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡- የጥምቀት በዓልን ለማክበር ወደ ጎንደር የሚመጡ ቱሪስቶች የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክን እንዲጎበኙ ዝግጅት ማድረጉን የፓርኩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ባለፉት ስድስት ወራት ፓርኩን የጎበኙ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ቁጥር መሻሻል ማሳየቱም ተጠቁሟል፡፡

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ማሩ ቢያድግልኝ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ የፓርኩን የቱሪስት ፍሰት ለመጨመር በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ መገናኛ ዘዴዎች ፓርኩን የማስተዋወቅ ስራ እየተከናወነ ነው፡፡

በጥምቀት በዓል በርካታ ቱሪስቶች ወደ ጎንደርና አካባቢው የሚመጡበት አመቺ ወቅት መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚሁ አጋጣሚ ጎብኚዎች ፓርኩን እንዲጎበኙ ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል፡፡

የፓርኩ መዳረሻ የሆኑ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ጥገናን ጨምሮ የጎብኚዎችን ምቾት መጠበቅ የሚያስችሉ የቱሪስት ማረፊያ ስፍራዎችን መሰረተ ልማት የማሟላት ስራ መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡

በአካባቢው የሰፈነው ሰላም ለቱሪስቶች ቁጥር መጨመር አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቅሰው፤ ባለፉት ስድስት ወራትም አንድ ሺህ የሚጠጉ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ፓርኩን መጎብኘታቸውን አስረድተዋል፡፡

ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ወቅት ከ400 የማይበልጡ ጎብኚዎች ፓርጉን መጎብኘታቸውን አስታውሰው፤ ሆኖም ዘንድሮ የቱሪስቶች ቁጥር መሻሻል የታየበትና ተስፋ ሰጪ እንደሆነም አመልክተዋል፡፡

ቱሪስቶቹ ከእስራኤል፣ ከፖላንድ፣ ከአሜሪካ፣ ከታይላድና ከቻይና የመጡ ሲሆን የአካባቢው ማህበረሰብም ለቱሪስቶች በሰጠው አገልግሎት ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡

ፓርኩ ከመግቢያ ትኬትና ከፊልም አገልግሎት ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል፡፡

የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ የሚያራዝሙና ፍሰቱንም ለመጨመር የሚያግዙ የቱሪዝም ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል፡፡

ፓርኩ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ዋልያ፤ ቀይ ቀበሮና ጭላዳ ዝንጀሮን ጨምሮ የብርቅዬ የዱር እንስሳትና አዕዋፋት መገኛ ስፍራ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026