የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>የጥምቀት በዓልን ለማክበር ወደ ጎንደር የሚመጡ ቱሪስቶች ፓርኩን እንዲጎበኙ ዝግጅት ተደርጓል</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡- የጥምቀት በዓልን ለማክበር ወደ ጎንደር የሚመጡ ቱሪስቶች የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክን እንዲጎበኙ ዝግጅት ማድረጉን የፓርኩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ባለፉት ስድስት ወራት ፓርኩን የጎበኙ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ቁጥር መሻሻል ማሳየቱም ተጠቁሟል፡፡

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ማሩ ቢያድግልኝ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ የፓርኩን የቱሪስት ፍሰት ለመጨመር በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ መገናኛ ዘዴዎች ፓርኩን የማስተዋወቅ ስራ እየተከናወነ ነው፡፡

በጥምቀት በዓል በርካታ ቱሪስቶች ወደ ጎንደርና አካባቢው የሚመጡበት አመቺ ወቅት መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚሁ አጋጣሚ ጎብኚዎች ፓርኩን እንዲጎበኙ ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል፡፡

የፓርኩ መዳረሻ የሆኑ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ጥገናን ጨምሮ የጎብኚዎችን ምቾት መጠበቅ የሚያስችሉ የቱሪስት ማረፊያ ስፍራዎችን መሰረተ ልማት የማሟላት ስራ መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡

በአካባቢው የሰፈነው ሰላም ለቱሪስቶች ቁጥር መጨመር አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቅሰው፤ ባለፉት ስድስት ወራትም አንድ ሺህ የሚጠጉ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ፓርኩን መጎብኘታቸውን አስረድተዋል፡፡

ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ወቅት ከ400 የማይበልጡ ጎብኚዎች ፓርጉን መጎብኘታቸውን አስታውሰው፤ ሆኖም ዘንድሮ የቱሪስቶች ቁጥር መሻሻል የታየበትና ተስፋ ሰጪ እንደሆነም አመልክተዋል፡፡

ቱሪስቶቹ ከእስራኤል፣ ከፖላንድ፣ ከአሜሪካ፣ ከታይላድና ከቻይና የመጡ ሲሆን የአካባቢው ማህበረሰብም ለቱሪስቶች በሰጠው አገልግሎት ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡

ፓርኩ ከመግቢያ ትኬትና ከፊልም አገልግሎት ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል፡፡

የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ የሚያራዝሙና ፍሰቱንም ለመጨመር የሚያግዙ የቱሪዝም ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል፡፡

ፓርኩ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ዋልያ፤ ቀይ ቀበሮና ጭላዳ ዝንጀሮን ጨምሮ የብርቅዬ የዱር እንስሳትና አዕዋፋት መገኛ ስፍራ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026