
ጎንደር፤ ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡- የጥምቀት በዓልን ለማክበር ወደ ጎንደር የሚመጡ ቱሪስቶች የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክን እንዲጎበኙ ዝግጅት ማድረጉን የፓርኩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
ባለፉት ስድስት ወራት ፓርኩን የጎበኙ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ቁጥር መሻሻል ማሳየቱም ተጠቁሟል፡፡
የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ማሩ ቢያድግልኝ ለኢዜአ እንደገለፁት፤ የፓርኩን የቱሪስት ፍሰት ለመጨመር በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ መገናኛ ዘዴዎች ፓርኩን የማስተዋወቅ ስራ እየተከናወነ ነው፡፡
በጥምቀት በዓል በርካታ ቱሪስቶች ወደ ጎንደርና አካባቢው የሚመጡበት አመቺ ወቅት መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚሁ አጋጣሚ ጎብኚዎች ፓርኩን እንዲጎበኙ ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል፡፡
የፓርኩ መዳረሻ የሆኑ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ጥገናን ጨምሮ የጎብኚዎችን ምቾት መጠበቅ የሚያስችሉ የቱሪስት ማረፊያ ስፍራዎችን መሰረተ ልማት የማሟላት ስራ መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡
በአካባቢው የሰፈነው ሰላም ለቱሪስቶች ቁጥር መጨመር አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቅሰው፤ ባለፉት ስድስት ወራትም አንድ ሺህ የሚጠጉ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ፓርኩን መጎብኘታቸውን አስረድተዋል፡፡
ባለፈው ዓመት በተመሳሳይ ወቅት ከ400 የማይበልጡ ጎብኚዎች ፓርጉን መጎብኘታቸውን አስታውሰው፤ ሆኖም ዘንድሮ የቱሪስቶች ቁጥር መሻሻል የታየበትና ተስፋ ሰጪ እንደሆነም አመልክተዋል፡፡
ቱሪስቶቹ ከእስራኤል፣ ከፖላንድ፣ ከአሜሪካ፣ ከታይላድና ከቻይና የመጡ ሲሆን የአካባቢው ማህበረሰብም ለቱሪስቶች በሰጠው አገልግሎት ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡
ፓርኩ ከመግቢያ ትኬትና ከፊልም አገልግሎት ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸዋል፡፡
የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ የሚያራዝሙና ፍሰቱንም ለመጨመር የሚያግዙ የቱሪዝም ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል፡፡
ፓርኩ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ዋልያ፤ ቀይ ቀበሮና ጭላዳ ዝንጀሮን ጨምሮ የብርቅዬ የዱር እንስሳትና አዕዋፋት መገኛ ስፍራ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡
አዲስ አበባ፣ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስከ ፈረንጆቹ 2049 ድረስ የሚተገበር የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ማስ...
Jul 28, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 16/2018 (ኢዜአ) ፦የኢትዮጵያ መንገድ መሰረተ ልማቶች የሕዝብን የኢኮኖሚ ትስስር በማሳለጥ የብልፅግና ድልድይ እየገነቡ መሆኑን የከተማ...
Jul 24, 2026
ጅማ፤ ሐምሌ 14/2018(ኢዜአ)፦ በጅማ ዞን የሩዝ ሰብልን ለማስፋፋት በተከናወነው ሥራ ምርታማነቱ እያደገ መምጣቱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገልጿል። በዞኑ...
Jul 22, 2026
ደብረ ብርሃን ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ199 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ 72 ኪሎ ሜትር የጠ...
Jul 18, 2026