የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በከተማዋ የኮሪደር ልማቱ ገፅታን ከመቀየር ባለፈ ጠንካራ የሥራ ባህልን እያጎለበተ ነው</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፤ ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡- በሚዛን አማን ከተማ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ጠንካራ የሥራ ባህልን እያጎለበተ መሆኑን የከተማዋ አስተዳደር አስታወቀ።

በከተማዋ በተለያዩ ምዕራፎች 34 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት እቅድ ተይዞ ወደ ተግባር የተገባ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ አካል የሆነው የሦስት ኪሎ ሜትር ልማት ሥራ በ130 ሚሊዮን ብር የሚከናወን ይሆናል።


የከተማዋ ከንቲባ አቶ ግሩም ተማም እንደገለፁት፤ የከተማዋን መልካም ገጽታ ከፍ የሚያደርገው የኮሪደር ልማት ሥራ ጠንካራ የሥራ ባህልን እያጎለበተ ነው።

ከተማዋን ጽዱና ምቹ የመኖሪያ ቦታ ከማድረግ ባለፈ የቱሪዝምና የኮንፍረንስ ማዕከል ማድረግ የሚያስችል ተግባር በመከናወን ላይ መሆኑንም ገልጸዋል።

ሥራው በፍጥነትና በጥራት ተጠናቆ ለትውልድ እንዲሻገር የሚያስችል ቁጥጥር በባለሙያዎች እና አመራሮች እየተደረገ ነው ብለዋል።

በ34 ኪሎ ሜትሩ የኮሪደር ልማት ሥራ ነባር መንገዶችን የማስፋት፣ የእግረኛ መንገድ ግንባታና የአዲስ መንገድ ከፈታ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችን የሚያካትት መሆኑን አክለዋል።

የኮሪደር ልማት ሥራውም በኅብረተሰብ ተሳትፎ የሚከናወን መሆኑን ገልፀው የሀብት ማሰባሰብ ሥራው መጀመሩንም አቶ ግሩም ጠቁመዋል።


የኮሪደር ልማት ሥራው ለበርካቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር የሥራ ትጋትን እየጨመረ ነው ያሉት ደግሞ የሚዛን አማን ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ቤሪ ናቸው።

ልማቱ በተጀመረ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ከ3 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል እንደተፈጠረ ገልጸው፤ በየቀኑ ከ250 በላይ ሠራተኞች ይሰማራሉ ብለዋል።


በኮሪደር ልማቱ የስራ ዕድል ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል አቶ መንግሥቱ መስፍን፤ በማታ የግንባታ ሥራ ሠርተው ባያውቁም በዚህ የልማት ሥራ ግን መሥራት መጀመራቸውን ገልጸዋል።

በዚህም ከማገኘው ገቢ ባሻገር የልማት ሥራውን በትጋትና በእኔነት ስሜት እየሰራሁ ለልጆቻችን ተሻጋሪ ልማትን ለማሳለፍ የኮሪደር ልማቱ ዕድልን ፈጥሮልኛል ሲሉ ተናግረዋል።


በልማቱ ምክንያት የስራ ዕድል ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ፤ ማታ ጭምር በመስራት የስራ ባህላቸውን ማሳደግ እንደቻሉም ገልፀዋል።

ሥራውን በተያዘለት ጊዜ ማጠናቀቅ ለራሳችንና ለሕዝባችን የሚጠቅም መሆኑን አውቀን ሙሉ ጊዜያችንን በሥራ እያሳለፍን ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026