የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በከተማዋ የኮሪደር ልማቱ ገፅታን ከመቀየር ባለፈ ጠንካራ የሥራ ባህልን እያጎለበተ ነው</p>

Jan 14, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፤ ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡- በሚዛን አማን ከተማ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ጠንካራ የሥራ ባህልን እያጎለበተ መሆኑን የከተማዋ አስተዳደር አስታወቀ።

በከተማዋ በተለያዩ ምዕራፎች 34 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት እቅድ ተይዞ ወደ ተግባር የተገባ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ አካል የሆነው የሦስት ኪሎ ሜትር ልማት ሥራ በ130 ሚሊዮን ብር የሚከናወን ይሆናል።


የከተማዋ ከንቲባ አቶ ግሩም ተማም እንደገለፁት፤ የከተማዋን መልካም ገጽታ ከፍ የሚያደርገው የኮሪደር ልማት ሥራ ጠንካራ የሥራ ባህልን እያጎለበተ ነው።

ከተማዋን ጽዱና ምቹ የመኖሪያ ቦታ ከማድረግ ባለፈ የቱሪዝምና የኮንፍረንስ ማዕከል ማድረግ የሚያስችል ተግባር በመከናወን ላይ መሆኑንም ገልጸዋል።

ሥራው በፍጥነትና በጥራት ተጠናቆ ለትውልድ እንዲሻገር የሚያስችል ቁጥጥር በባለሙያዎች እና አመራሮች እየተደረገ ነው ብለዋል።

በ34 ኪሎ ሜትሩ የኮሪደር ልማት ሥራ ነባር መንገዶችን የማስፋት፣ የእግረኛ መንገድ ግንባታና የአዲስ መንገድ ከፈታ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችን የሚያካትት መሆኑን አክለዋል።

የኮሪደር ልማት ሥራውም በኅብረተሰብ ተሳትፎ የሚከናወን መሆኑን ገልፀው የሀብት ማሰባሰብ ሥራው መጀመሩንም አቶ ግሩም ጠቁመዋል።


የኮሪደር ልማት ሥራው ለበርካቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር የሥራ ትጋትን እየጨመረ ነው ያሉት ደግሞ የሚዛን አማን ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ቤሪ ናቸው።

ልማቱ በተጀመረ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ከ3 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል እንደተፈጠረ ገልጸው፤ በየቀኑ ከ250 በላይ ሠራተኞች ይሰማራሉ ብለዋል።


በኮሪደር ልማቱ የስራ ዕድል ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል አቶ መንግሥቱ መስፍን፤ በማታ የግንባታ ሥራ ሠርተው ባያውቁም በዚህ የልማት ሥራ ግን መሥራት መጀመራቸውን ገልጸዋል።

በዚህም ከማገኘው ገቢ ባሻገር የልማት ሥራውን በትጋትና በእኔነት ስሜት እየሰራሁ ለልጆቻችን ተሻጋሪ ልማትን ለማሳለፍ የኮሪደር ልማቱ ዕድልን ፈጥሮልኛል ሲሉ ተናግረዋል።


በልማቱ ምክንያት የስራ ዕድል ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ፤ ማታ ጭምር በመስራት የስራ ባህላቸውን ማሳደግ እንደቻሉም ገልፀዋል።

ሥራውን በተያዘለት ጊዜ ማጠናቀቅ ለራሳችንና ለሕዝባችን የሚጠቅም መሆኑን አውቀን ሙሉ ጊዜያችንን በሥራ እያሳለፍን ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026