
ሚዛን አማን፤ ጥር 5/2017(ኢዜአ)፡- በሚዛን አማን ከተማ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ጠንካራ የሥራ ባህልን እያጎለበተ መሆኑን የከተማዋ አስተዳደር አስታወቀ።
በከተማዋ በተለያዩ ምዕራፎች 34 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት እቅድ ተይዞ ወደ ተግባር የተገባ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ አካል የሆነው የሦስት ኪሎ ሜትር ልማት ሥራ በ130 ሚሊዮን ብር የሚከናወን ይሆናል።

የከተማዋ ከንቲባ አቶ ግሩም ተማም እንደገለፁት፤ የከተማዋን መልካም ገጽታ ከፍ የሚያደርገው የኮሪደር ልማት ሥራ ጠንካራ የሥራ ባህልን እያጎለበተ ነው።
ከተማዋን ጽዱና ምቹ የመኖሪያ ቦታ ከማድረግ ባለፈ የቱሪዝምና የኮንፍረንስ ማዕከል ማድረግ የሚያስችል ተግባር በመከናወን ላይ መሆኑንም ገልጸዋል።
ሥራው በፍጥነትና በጥራት ተጠናቆ ለትውልድ እንዲሻገር የሚያስችል ቁጥጥር በባለሙያዎች እና አመራሮች እየተደረገ ነው ብለዋል።
በ34 ኪሎ ሜትሩ የኮሪደር ልማት ሥራ ነባር መንገዶችን የማስፋት፣ የእግረኛ መንገድ ግንባታና የአዲስ መንገድ ከፈታ እንዲሁም የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችን የሚያካትት መሆኑን አክለዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራውም በኅብረተሰብ ተሳትፎ የሚከናወን መሆኑን ገልፀው የሀብት ማሰባሰብ ሥራው መጀመሩንም አቶ ግሩም ጠቁመዋል።

የኮሪደር ልማት ሥራው ለበርካቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር የሥራ ትጋትን እየጨመረ ነው ያሉት ደግሞ የሚዛን አማን ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ቤሪ ናቸው።
ልማቱ በተጀመረ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ከ3 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል እንደተፈጠረ ገልጸው፤ በየቀኑ ከ250 በላይ ሠራተኞች ይሰማራሉ ብለዋል።

በኮሪደር ልማቱ የስራ ዕድል ተጠቃሚ ከሆኑት መካከል አቶ መንግሥቱ መስፍን፤ በማታ የግንባታ ሥራ ሠርተው ባያውቁም በዚህ የልማት ሥራ ግን መሥራት መጀመራቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ከማገኘው ገቢ ባሻገር የልማት ሥራውን በትጋትና በእኔነት ስሜት እየሰራሁ ለልጆቻችን ተሻጋሪ ልማትን ለማሳለፍ የኮሪደር ልማቱ ዕድልን ፈጥሮልኛል ሲሉ ተናግረዋል።

በልማቱ ምክንያት የስራ ዕድል ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ፤ ማታ ጭምር በመስራት የስራ ባህላቸውን ማሳደግ እንደቻሉም ገልፀዋል።
ሥራውን በተያዘለት ጊዜ ማጠናቀቅ ለራሳችንና ለሕዝባችን የሚጠቅም መሆኑን አውቀን ሙሉ ጊዜያችንን በሥራ እያሳለፍን ነው ብለዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026